የሩሲያ የአንድነት፣ የአብሮነት እና የጋራ መረዳዳት እሴቶች ከአፍሪካ የኡቡንቱ ፍልስፍና ጋር ይጣጣማሉ - ላቭሮቭ
18:28 18.12.2025 (የተሻሻለ: 18:34 18.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ የአንድነት፣ የአብሮነት እና የጋራ መረዳዳት እሴቶች ከአፍሪካ የኡቡንቱ ፍልስፍና ጋር ይጣጣማሉ - ላቭሮቭ
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ አጋርነት ፎረም የሚኒስትሮች ጉባኤን አስመልከቶ በአፍሪካ ሚዲያ ላይ ባወጡት ጽሁፍ፤ ሩሲያ እና አፍሪካ የእያንዳንዳቸውን ስልጣኔ ባህሪያት እያከበሩ ወዳጅነትንና ትብብርን እንደሚያዳብሩ አንስተዋል።
"ለሕዝቦቻችን ደህንነት ገንቢ እና ነገን ያማተረ አጋርነት ወሳኝ ነው። በካይሮ የሚደረገው የሚኒስትሮች ስብሰባ ለ2026ቱ ሶስተኛው የሩሲያ–አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ መሠረት እንደሚጥል እና አዲስ ኃይል እንደሚሰጠው እርግጠኛ ነኝ።"
እንደ ላቭሮቭ ገለጻ፤ ሁለት የሩሲያ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤዎች "በተሳካ ሁኔታ ተካሂደዋል"፦
በሶቺ በ2019
በሴንት ፒተርስበርግ በ2023
ፎረሙ "በተለይም በሁለትዮሽ ደረጃ በፍጥነት እያደጉ ያሉ የሩሲያ እና አፍሪካ ሀገራት ግንኙነቶችን ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ ያሟላል እንዲሁም ያሳድጋል" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X