በኢትዮጵያ የመጀመሪያው በመግነጢሳዊ ኃይል የነርቭ ሴሎችን በማነቃቀት የሚሰጥ የጭንቀት ህክምና አገልግሎት በይፋ ተጀመረ
18:09 18.12.2025 (የተሻሻለ: 18:14 18.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው በመግነጢሳዊ ኃይል የነርቭ ሴሎችን በማነቃቀት የሚሰጥ የጭንቀት ህክምና አገልግሎት በይፋ ተጀመረ
በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የሚሰጠው ህክምና በመድኃኒት ወይም በሥነ-ልቦና ምክር ህክምና ለውጥ ላላሳዩ ታካሚዎች እንደሚያገለግል ተገልጿል።
ይህ ዘመናዊ የጭንቀት ህክምና መግነጢሳዊ ሞገዶችን ወደ አንጎል በመላክ የአእምሮ እና የነርቭ ችግሮችን ያለ ቀዶ ጥገና የሚያስተካክል መሆኑን የኮሌጁ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉቀን ተስፋዬ ተናግረዋል።
ህክምናውን ለማስጀመር የሆስፒታሉ ስፔሻሊስት ሐኪሞች በጀርመን ሙኒክ በሚገኝ ተቋም ከፍተኛ ሥልጠና ወስደው መመለሳቸውንም ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X