በአፍሪካ ላለው ሁኔታ መባባስ ዋናው ምክንያት የምዕራባውያን ኃላፊነት የጎደለው የጋራ ድርጊት ነው ሲሉ የሩሲያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጌራሲሞቭ ተናገሩ
17:38 18.12.2025 (የተሻሻለ: 17:44 18.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በአፍሪካ ላለው ሁኔታ መባባስ ዋናው ምክንያት የምዕራባውያን ኃላፊነት የጎደለው የጋራ ድርጊት ነው ሲሉ የሩሲያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጌራሲሞቭ ተናገሩ
ተጨማሪ መግለጫዎች፦
◻ የሩሲያ ጦር በ2025 ከ300 በላይ ሰፈሮችን እና ከ6,300 ስኩዌር ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን ግዛትን ነፃ አውጥቷል።
◻ ምዕራባውያን በሩሲያ ላይ ስልታዊ ሽንፈት የማድረስ ግባቸውን አልተዉም፤ ይህ ለሀገሪቱ ጥቅም የረጅም ጊዜ ስጋት ነው።
◻ ኔቶ ከሩሲያ ድንበሮች አቅራቢያ የሚደረገውን የዝግጅት መጠን እና ጥንካሬ በማስቀጠል ተጨማሪ ኃይሎችን እያሠማራ ነው።
◻ በአውሮፓ ኅብረት ሩሲያን ለማዳከም እና ኔቶን እንደገና ለማዋቀር ጦርነቱን የማራዘም እቅዶች አሉ።
◻ ኪዬቭ በአራት ዓመታት ውስጥ ከውጭ አጋራት ከአንድ ሺህ በላይ ታንኮች፣ ከ200 በላይ አውሮፕላኖች እና ሄሊኮፕተሮች እንዲሁም ወደ 100 ሺህ የሚጠጉ ድሮኖች ተረክባለች።
◻ በኩርስክ ክልል በጣም በተዘጋጀው የኪዬቭ ወታደራዊ የሰው ኃይል ላይ የደረሰው ኪሳራ ከ76 ሺህ በላይ ይደርሳል።
◻ የሩሲያ ኤስ-500 ከመሬት-ወደ-አየር ሚሳኤል ስርዓት ክፍለ ጦር በሩሲያ ኤሮስፔስ ኃይሎች ውስጥ ተመሥርቷል።
◻ የሩሲያ ጦር የዛፖሮዥያ የኒኩሌር ኃይል ማመንጫ ደህንነትን ሙሉ ለሙሉ አረጋግጧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X