ናይጄሪያ የቡርኪና ፋሶን የአየር ክልል በመጣሷ ይቅርታ ጠየቀች
16:45 18.12.2025 (የተሻሻለ: 16:54 18.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ናይጄሪያ የቡርኪና ፋሶን የአየር ክልል በመጣሷ ይቅርታ ጠየቀች
የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዩሱፍ ማይታማ ቱጋር በአሠራር ሂደት ክፍተት በቡርኪና ፋሶ በድንገት ለማረፍ ስለተገደደው የናይጄሪያ አውሮፕላን ይቅርታ እንደጠየቁ የቡርኪናቤ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ቱጋር በተጨማሪም አንድ የናይጄሪያ ባለሥልጣን በቡርኪናቤ ወታደሮች ተፈጽሟል ስላሉት አያያዝ የሰጡትን "ተገቢ ያልሆነ አስተያየት" በማውገዝ ውድቅ አድርገዋል።
ሚነስትሩ ቡርኪና ፋሶ የአውሮፕላኑን ሠራተኞች ወንድማዊ በሆነ መንገድ በመያዟ እና ሀገሪቱ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ያስመዘገበችውን ስኬቶች አድንቀዋል ሲል የፕሬዝዳንት ጽ/ቤቱ አስታውቋል።
ሁለቱ ወገኖች የፀጥታ ጉዳዮችን ጨምሮ ክልላዊ ትብብርን ማጠናከር በተመለከተ ተወያይተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


