የአፍሪካ ልማት ባንክ ለ17ኛው የአፍሪካ ልማት ፈንድ የሀብት ማሟያ መርሃ-ግብር 11 ቢሊዮን ዶላር አገኘ
16:40 18.12.2025 (የተሻሻለ: 16:44 18.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለ17ኛው የአፍሪካ ልማት ፈንድ የሀብት ማሟያ መርሃ-ግብር 11 ቢሊዮን ዶላር አገኘ
ይህም በፈንዱ የ50 ዓመታት ታሪክ ውስጥ ከፍተኛው የገንዘብ መጠን ነው ተብሏል።
አርባ ሦስት አጋሮች ከቀደመው የፈንድ ማሟያ ጋር ሲነጻጸር የ23 በመቶ ጭማሪ ለታየበት የገንዘብ መጠን ቃል ገብተዋል። ይህም ዓለም አቀፍ ዕርዳታ እየቀነሰ ባለበት ወቅት የተገኘ እንደሆነ የአፍሪካ ልማት ባንክ አስታውቋል።
እንደ ባንኩ ገለፃ፤ ጥቅሉ ከኦፔክ የዓለም አቀፍ ልማት ፈንድ እና በአፍሪካ የአረብ ባንክ የኢኮኖሚ ልማት የሚጠበቁ መዋጮዎችን እንዲሁም 23 የአፍሪካ ሀገራት ቃል የገቡትን 182.7 ሚሊዮን ዶላር ያካትታል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ 19ኙ ለፈንዱ አነስተኛ የወለድ መጠን የብድር መስኮት ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋጽኦ ያደረጉ ናቸው።
“ይህ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በልማት ፋይናንስ ዙሪያ እጅግ ፈታኝ ከሆኑት ዓለም አቀፍ ሁኔታዎች በአንዱ፤ አጋሮቻችን ከወጪ ቅነሳ ይልቅ ራዕይን፤ ምንም ካለማድረግ ኢንቨስትመንትን መርጠዋል” ሲሉ የባንኩ ፕሬዚዳንት ሲዲ ኦውልድ ታህ ተናግረዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X