የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ በዩክሬን የሰላም ሂደት የፕሬዝዳንት ትራምፕን አካሄድ እንጂ ሞስኮን አይወክሉም - ክሬምሊን
15:33 17.12.2025 (የተሻሻለ: 15:34 17.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ በዩክሬን የሰላም ሂደት የፕሬዝዳንት ትራምፕን አካሄድ እንጂ ሞስኮን አይወክሉም - ክሬምሊን
ከክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ መግለጫዎች የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
◻ ከሞስኮ ጋር በሚኖር በእያንዳንዱ አዲስ ግንኙነት፤ ዊትኮፍ የሩሲያን አቋም ለመረዳት የተሻለ እድል ያገኛሉ፡፡
◻ ክሬምሊን የአሜሪካ ወገን ዝግጁ ሲሆን ከዩክሬን እና ከአውሮፓ ጋር በሰላም ሂደቱ ዙሪያ የሚያደረገውን ውይይት ውጤት እንደሚያቀርብ ይጠብቃል፡፡
◻ ክሬምሊን በአሜሪካ ሊጣሉ ስለሚችሉ አዳዲስ ማዕቀቦች ሪፖርቶችን አልተመለከተም፤ ነገር ግን እንደዚህ ያሉ እቅዶች በዋሽንግተን እንደሚንሸራሸሩ መረጃዉ አለው፡፡
◻ ማዕቀቦች ለግንኙነቶች እንቅፋት ናቸው፡፡
◻ ዘለንስኪ ምን ያህል ሰላምን እንደሚፈልግ ከአውሮፓ ኅብረት እና ከኪዬቭ የሰላም ሰነዶች በኋላ ግልጽ ይሆናል፡፡
◻ ምዕራባውያን ኃይሎችን ዩክሬን ውስጥ በማሰማራት ዙሪያ የሩሲያ አቋም ወጥ እና የታወቀ ነው፡፡
◻ ሩሲያ የዩክሬን የሰላም እቅድን የተመለከቱ ጉዳዮች በሚዲያ በኩል አትወያይም፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X