- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

አፍሪካን ከውስጥ ወደ ውጭ መገንባት፡ ባህል፣ ገንዘብ (ምንዛሪ) እና የኃይል ትስስር

አፍሪካን ከውስጥ ወደ ውጭ መገንባት፡ ባህል፣ ገንዘብ (ምንዛሪ) እና የኃይል ትስስር
ሰብስክራይብ
“በእኛ የሥነ ምግባር እሴቶች ላይ በመመሥረት፣ ለህብረተሰቦቻችንና ለኅብረተሰባችን ጥሩ የሆነውንና አስፈላጊ የሆነውን ነገር መከላከል አለብን። በትክክለኛ መረጃ እና በተገቢው ግንኙነት በትክክል መከላከል አለብን። […]የመንግሥት መዋቅር በሽማግሌዎች ላይ እምነት ሊኖረውና ሥልጣንን በአግባቡ መወከል አለበት፤ ዝም ብሎ በስም ብቻ ሳይሆን።” ሲሉ የኢትዮጵያ የሽማግሌዎች ምክር ቤት ሊቀመንበር የሆኑት ተስፋጽዮን ደለለው (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሦስት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል የኢትዮጵያ የሽማግሌዎች ምክር ቤት ሊቀመንበር ተስፋጽዮን ደለለው (ዶ/ር) ጋር ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች ሰላምን መገንባትና ማንነትን መጠበቅበተመለከተ ሚናቸውን እንቃኛለን፡፡ በሁለተኛውም ክፍል ደግሞ የፓን-አፍሪካ የክፍያ ሥርዓትና እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያን የዲጂታል ፋይናንስ ስትራቴጂ ተስፋዎችን ለአፍሪካ የፋይናንስ ሉዓላዊነት ያላቸውን ሚና እንቃኛለን፡፡ በመጨረሻውም ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዘርፍ በተገኙ ግንዛቤዎች የአፍሪካን የኃይል ተቃርኖ እንመረምራለን ለዚህም በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልገሎት የ 'ኤኤምአይና ስካዳ' ሥራ አስኪያጅ ከአቶ ዘሪሁን አበበ ጋር ባደረነው ውይይት ዳስሰነዋል፡፡

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡
አዳዲስ ዜናዎች
0