- Sputnik አፍሪካ, 1920
Continental Drift
Continental Drift' በአፍሪካ ቅርፅ እየቀየሩ ያሉትን እንደዚሁም የአለም የደቡብን ክፍል ሚና በአዲስ መልክ እየገለጹ ያሉትን ስር ነቀል ለውጦች የሚከታተል ፕሮግራም ነው።ትዕይንቱ ፖሊሲዎች፣ ገበያዎች እና ፈጠራዎች ከዕለት ተዕለት ሕይወት ጋር እንዴት እንደሚገናኙ በመመርመር በእውነታ ላይ የተመሰረቱ ግንዛቤዎችን እና ትክክለኛ የአፍሪካ አመለካከቶችን ያቀርባል።

ኃይል፣ ትብብር እና ምርት፡ የአፍሪካ አዲሱ የሉዓላዊነት መንገድ

ኃይል፣ ትብብር እና ምርት፡ የአፍሪካ አዲሱ የሉዓላዊነት መንገድ
ሰብስክራይብ
"[...] የብሪክስ ቁልፍ መርህ የሉዓላዊነትን ማስከበር፣ የሀገራዊ ሁኔታዎችን እና ነባራዊ እውነታዎችን ማክበር ነው። በኢነርጂ ዘርፉም ቢሆን የምናደርገው ትብብር ይህንን ያገናዘበ ነው።" ሲሉ የሩሲያ የኢነርጂ ኤጀንሲ ተወካይ አናስታሲያ ሺሮኮግራድ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ ሶስት የተለያዩ ወሳኝ ጉዳዮችን እንመለከታለን በቀዳሚነ የብሪክስ የኢነርጂ ትብብር ለኢትዮጵያ ምን ይዞ መጥቷል ፣ ለአፍሪካ የኢነርጂ ሉዓላዊነትስ ምን ማለት ነው ስንል የሩሲያ ኢነርጂ ኤጀንሲ ተወካይ አናስታሲያ ሺሮኮግራድ አነጋግረናቸዋል፡፡ በሁለተኛው ክፍል ከታህሳስ 2 እስከ 3 በአዲስ አበባ የተካሄደውን የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ መነሻ አድርገን አፍሪካንና የሃይል ትስስርን እንዲሁም የብሪክስ ጥምረትን ሚና ከኬንያ ኢነርጂ ሚኒስቴር የታዳሽ ኃይል ረዳት ዳይሬክተር ጆርጅ ኒዮንጋዮ፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክ የኢነርጂ ብቃት ባለሙያ ጃሌል ቻብቹብ እና ከሌሎች የጉባዔው ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን ጠይቀናል። የሀገር ውስጥ አምራቾች የገበያውን ክፍተት እንዴት እየሸፈኑ ነው? የቅመም ዕፅዋት ውጤቶች መስራች መቅደላዊት ያሬድ እና ዲዛይነት ቤተልሄም ጌታቸው ያነጋገንበት ጉዳይም በዚሁ መሰናዶ ውስጥ ተካትቷል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0