- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

የፀረ ቅኝ ግዛት ቀን፡ የከሰመው ግን መልኩን ለውጦ የመጣው ቅኝ ግዛት ሲገመገም

የፀረ ቅኝ ግዛት ቀን፡ የከሰመው ግን መልኩን ለውጦ የመጣው ቅኝ ግዛት ሲገመገም
ሰብስክራይብ
''አፍሪካ ትናንት በቅኝ ግዛት የደረሰባት ነገር አይዘነጋም፣ ራስ ገዝ እና ሉዓላዊነት በሌለበት ነፃነት አይኖርም። በዚህም ሀገራት የራሳቸውን ነፃነት የማወጅ ሙሉ መብት አላቸው — የአፍሪካ ሆኑ ሌሎች ሀገራት ባለፉ ዘመናት በምዕራባውያን ከደረሰባቸው ተፅዕኖ አንፃር ወደፊት ሌሎች አማራጮችን በጂዮ ፖለቲካው ላይ መቃኘት ይኖርባቸዋል '' ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መምህሩ የእዮብዘር ዘውዴ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ሁለት አንኳር ጉዳዮችን በምንቃኝበት ፕሮግራማችን፣ በመጀመሪያው ክፍል ዓለም አቀፉ የፀረ ቅኝ ግዛት ቀንን መነሻ በማድረግ ዕለቱን ለውጥ ለማምጣትና መልኩን የቀየረውን ቅኝ ግዛትን በተመለከተ ለመወያየት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መምህሩ የእዮብዘር ዘውዴን ጋብዘናቸዋል። ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ በአፍሪካ ትብብርን፣ ሰላም ግንባታን እንዲሁም አስተማማኝ ልማትን ለመፍጠር ሁነኛ የዲፕሎማሲ መድረክ መሆን በሚችልበት ጉዳይ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የጂኦስፓሻል አስተዳደር ክፍል መሪ አንድሬይ ኖምጉዊሮማ እንዲሁም በኢትዮጵያ ስፔስና ጂኦስፓሻል ተቋም ምክትል ዳይሬክተር ዩሽሩን አለማየሁ (ዶ/ር) ጋር ያደረግነው ቆይታም በፕሮግራሙ ሁለተኛው ክፍል የምንቃኘው ሌላኛው ጉዳያችን ነው።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0