ጠረፍ የተወሰኑ ሀገራት ወይም የኃያላን ብቻ ሳይሆን የሁሉም ነው - የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱጠረፍ የተወሰኑ ሀገራት ወይም የኃያላን ብቻ ሳይሆን የሁሉም ነው - የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት
ጠረፍ የተወሰኑ ሀገራት ወይም የኃያላን ብቻ ሳይሆን የሁሉም ነው - የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 15.12.2025
ሰብስክራይብ

ጠረፍ የተወሰኑ ሀገራት ወይም የኃያላን ብቻ ሳይሆን የሁሉም ነው - የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት

በ2012 እና 2013 ዓ.ም ታህሳስ ወራት የመጀመሪያ እና ሁለተኛውን የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች ያመጠቀችው ኢትዮጵያ፤ የሚቀጠለው ዓመት መጨረሻ ኢቲ-አርኤስኤስ 2 የተሰኘውን ሦስተኛ ሳተላይት ወደ ጠረፍ ለመላክ እየሠራች ነው፡፡

“በእንጦጦ የሚገኘው የምድር ምልከታ ጣቢያ ሶስት አንቴናዎች አሉት። አንደኛው 5.4 ሜትር ነው። ሁሉም የምድር ምልከታ ሳተላይት ጣቢያዎች ናቸው። በሌሊት ሰማይ ለመመልከት የሚያገለግሉ ሁለት ቴሌስኮፖችም አሉን።...የአዋጭነት ጥናቶችን በማዘጋጀት እና የኮሚኒኬሽን ሳተላይት በመገንባት ወደ ሥራ ለማስገባት እየሠራን ነው” ሲሉ የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ይሽሩን አለማየሁ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው ጠፈር፤ ሳይንስ ብቻ ሳይሆን ጂኦፖለቲካዊ መልክ በመያዝ ፖለቲካዊ ጉዳይ ሊሆን እንደሚችልም ነው የተናገሩት፡፡

“በጠፈር ሳይንስ በምግብ ዋስትና፣ በሉዓላዊነት እና በሌሎች ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ መሥራት ይቻላል። በዋናነት የብሔራዊ ደህንነት እና የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ነው። ለዚህም ነው ወሳኝ ጉዳይ እየሆነ የመጣው። ሀገራት በተለይም በዚህ ባለብዙ ዋልታ ዓለም እጅ ለእጅ ተያይዘው መሥራት አለባቸው።”

አፍሪካ ከሌላው ዓለም አንጻር በዘርፉ ከኋላ እንደቀረችም አንስተዋል፡፡ እንደ ባለሥልጣኑ ገለጻ በምህዋር ላይ ከሚገኙት ከ10 ሺህ በላይ ሳተላይቶች 65 ብቻ የአፍሪካ ናቸው፡፡

“መጀመሪያ አካባቢ ሩሲያውያንና አሜሪካውያን ብቻ እርስ በርስ ይፎካከሩ ነበር። አሁን የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና በጠፈር እንቅስቃሴ ላይ የሚሠሩ አካላት የሚታዩበት ባለብዙ ዋልታ ዓለም ነው። ያለ ትብብር ዘላቂ ወይም ጥቅም የምናገኝበት አይሆንም። በአቅም ግንባታ፣ በመሠረተ ልማት ግንባታ እና በዲፕሎማሲ ረገድ ትብብር በጣም አስፈላጊ ነው።”

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0