ብሪክስ ለጥልቅ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ‘አዲስ ማዕቀፍ’ ያቀርባል - የኢራን ፕሬዝዳንት

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱብሪክስ ለጥልቅ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ‘አዲስ ማዕቀፍ’ ያቀርባል - የኢራን ፕሬዝዳንት
ብሪክስ ለጥልቅ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ‘አዲስ ማዕቀፍ’ ያቀርባል - የኢራን ፕሬዝዳንት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 14.12.2025
ሰብስክራይብ

ብሪክስ ለጥልቅ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ‘አዲስ ማዕቀፍ’ ያቀርባል - የኢራን ፕሬዝዳንት

ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን "ብሪክስ በብሔራዊ ሉዓላዊነት፣ በግዛት አንድነት እና በአገራት ብዝኃ ባሕሎች እና ሥልጣኔዎች ላይ የጋራ መከባበርን መሠረት ያደረገ አዲስ የኮሙኒኬሽን ማዕቀፍ (ሞዴል) ሊያቀርብ ይችላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ለፍትሐዊና ሚዛናዊ ትብብር መንገድ ሊጠርግ ይችላልም" ብለዋል።



ፕሬስ ቲቪ እንደዘገበው ፕሬዝዳንቱ አስተያየታቸውን የሰጡት በቴህራን ከኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይ ነው።

የኢራኑ መሪ አክለውም፣ ብሪክስ በማደግ ላይ እንዳሉ ኢኮኖሚዎች ስብስብነቱ፣ በዓለም አቀፍ ሥርዓት ውስጥ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መስተጋብርን በማሳደግ እና የአንድ ወገንን የበላይነት በመዋጋት ስትራቴጂያዊ ሚናን ይጫወታል።

ኢትዮጵያ እና ኢራን የብሪክስ አባል ናቸው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0