ዘለንስኪ በሙስና እና በፖለቲካዊ ተለዋዋጭነት "በመያዛቸው" ምክንያት ምርጫን አልቀበልም ብለዋል ፦ ፈረንሳያዊ ጋዜጠኛ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱዘለንስኪ በሙስና እና በፖለቲካዊ ተለዋዋጭነት "በመያዛቸው" ምክንያት ምርጫን አልቀበልም ብለዋል ፦ ፈረንሳያዊ ጋዜጠኛ
ዘለንስኪ በሙስና እና በፖለቲካዊ ተለዋዋጭነት በመያዛቸው ምክንያት ምርጫን አልቀበልም ብለዋል ፦ ፈረንሳያዊ ጋዜጠኛ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 14.12.2025
ሰብስክራይብ

ዘለንስኪ በሙስና እና በፖለቲካዊ ተለዋዋጭነት "በመያዛቸው" ምክንያት ምርጫን አልቀበልም ብለዋል ፦ ፈረንሳያዊ ጋዜጠኛ

የቅርብ ጊዜ የሙስና ቅሌቶችን ተክተሎ አሜሪካውያን የዩክሬን መሪን ከሥልጣን እንዲወርዱ ጫና ማድረግ ይፈልጋሉ ሲሉ ሎውረንት ብራያርድ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

“ከዘለንስኪ ጀርባ ያለው ሙሉ የሙስና ሥርዓት ነው። ዘለንስኪ አሁን ባለው ሁኔታ ሥልጣን የመልቀቅ ፍላጎት የላቸውም። ከሥልጣን እንደለቀቁ በእሳቸው ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ስለሚያገነዘቡ እስከ መጨረሻው መታገል ይሻሉ።”

እንደ ጋዜጠኛው ገለፃ፣ ዘለንስኪ ማንኛውንም ድርድር በሚቃወሙት ጽንፈኛ የቀኝ ዘመም ብሔርተኛ ክንፍም ታስረዋል።

“ዘለንስኪ ሙሉ በሙሉ ተይዘዋል (ወጥመድ ውስጥ ወድቀዋል)። ወደ ድርድር የሚገቡ ከሆነ በባንዴራውያን (የዩክሬን ጽንፈኛ ብሔርተኞች፣ የናዚ ተባባሪ የነበረው ስቴፓን ባንዴራ ወራሾች) ይያዛሉ። ወደ ድርድር ካልሄዱ ደግሞ የዶናልድ ትራምፕ እና የዩክሬን ብሔራዊ የፀረ-ሙስና ቢሮ ስጋት ይጠብቃቸዋል።"

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ሩሲያ ዐውደ ግንባር ላይ እየገሰገሰች እና ሴቨርስክ ከተለቀቀች በኋላ ወደ ስላቭያንስክ የሚወስደውን መንገድ እያስከፈተች ነው ሲል ጋዜጠኛው ደምድሟል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0