አሜሪካ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ የሰላም ስምምነትን ጥሳለች ስትል ሩዋንዳን ከሰሰች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
10:41 14.12.2025 (የተሻሻለ: 12:34 14.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ የሰላም ስምምነትን ጥሳለች ስትል ሩዋንዳን ከሰሰች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
የሩዋንዳ በምስራቃዊት ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ የምታደርጋቸው ድርጊቶች በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የተሸመገለውን "የዋሽንግተን ስምምነትን ግልጽ ጥሰት ናቸው" ሲሉ ማርኮ ሩቢዮ በኤክስ አካውንታቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ አስነብበዋል።
“አሜሪካ ለፕሬዝዳንቱ የተገቡት ቃሎች መፈፀማቸውን ለማረጋገጥ እርምጃ ትወስዳለች” ሲሉ ከፍተኛው ዲፕሎማት አስጠንቅቀዋል።
የሩቢዮ መግለጫ፣ አሜሪካ ዓርብ ዕለት በተባበሩት መንግሥታት በኩል ሩዋንዳ በምስራቃዊ ኮንጎ የኤም23 አማፂያንን በመደገፍ "አለመረጋጋት እና ጦርነትን እየቀሰቀሰች ነው" የሚል ክስ ተከትሎ የመጣ ነው።
ይህ ወቀሳ የመጣው የኮንጎ እና የሩዋንዳ መሪዎች ሕዳር 26 በአሜሪካ አደራዳሪነት በዋሽንግተን የሰላም ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X