🪖 የሴቨርስክ ምሽግ መፈራረስ ለዩክሬን ጦር 'ምቅሰፍት' ነው - ባለሙያ
19:32 13.12.2025 (የተሻሻለ: 19:54 13.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
🪖 የሴቨርስክ ምሽግ መፈራረስ ለዩክሬን ጦር 'ምቅሰፍት' ነው - ባለሙያ
ወታደራዊ ባለሙያው ኤቭጄኒ ሚካይሎቭ፣ “የሴቨርስክ መያዝ ለዩክሬን ጦር ኃይሎች መቅሰፍት ነው፤ ምክንያቱም ሩሲያን በዶንባስ በዩክሬን ቁጥጥር ስር ወደ ሚገኙና በከፍተኛ ሁኔታ ወደተጠናከሩት ክራማቶርስክ እና ስላቪያንስክ ወሳኝ ከተሞች ለመገስገስ ያስችላታል” ብለዋል።
እንደ ሚካይሎቭ የሴቨርስክ ነፃ መውጣት፦
1⃣ በአቅራቢያው አካባቢዎች ለሚገኙ የዩክሬን ኃይሎች የአቅርቦትና የሎጂስቲክስ መስመሮችን ይቆረጣል፤ ይህም “የውጊያ ቁሳቁስ እጥረት፣ በቂ ምግብ አለመኖር እና ወታደሮችን በየጊዜው መለዋወጥ አለመቻልን” ማለት ነው፡፡
2⃣ “በዩክሬን ጦር የመከላከል አቅም ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል፤ እናም ከአሁን በኋላ የሌሉ በደንብ የሰለጠኑ ክፍሎችን እንደገና ማሰማራት የማይቻል ያደርጋል፡፡”፤ የሰለጠኑ ወታደሮች እጥረት የዩክሬን የመከላከያ ደሕንነት (GUR) ልዩ ኃይሎች ኩፒያንስክን ለመያዝ መላካቸውን እና ጄኔራል ሲርስኪ ከዳተኞች በጥቃት ፈፃሚ ሰራዊት ውስጥ እንዲሰለፉ ትዕዛዝ መስጠታቸው ያሳያል፡፡
3⃣ የዩክሬን ወታደሮች ከያዟቸው የዶንባስ አካባቢዎች መልቀቅ በሰላም ድርድሩ አንዳንድ ስምምነቶች ላይ የነበሩትን ዕቅዶች ያናጋል፡፡
4⃣ በአገሪቱ አመራር ዙሪያ ባሉ ፖሊሲዎችና ቅሌቶች ምክንያት ቀድሞውንም እየቀነሰ የመጣውን የዩክሬን ሞራል የበለጠ ይዳክማል። ሚካይሎቭ ሲያጠቃልሉ፣ “ሞራላቸው ወርዷል፤ ወታደራዊ ዘመቻዎችን ለማካሄድ ያለው ሞራል ዝቅተኛ ከሆነ፣ አካባቢው የቱንም ያህል የተጠናከረ ቢሆን፣ የመቋቋም ፍላጎት ባለመኖሩ እና ድካም በመኖሩ ይወድቃል” ብለዋል።

© telegram sputnik_ethiopia
/