የዛምቢያ ሐኪሞች የጨቅላ ሕጻናት ሞት ምጣኔን ለመቀነስ ለሚያግዘው የሩሲያ ሥልጠና እውቅና ሰጡ
የዛምቢያ ሐኪሞች የጨቅላ ሕጻናት ሞት ምጣኔን ለመቀነስ ለሚያግዘው የሩሲያ ሥልጠና እውቅና ሰጡ
የሩሲያ ኩላኮቭ ብሔራዊ የሕክምና ምርምር ማዕከል፣ ሉሳካ ውስጥ “የእናት እና የሕጻናት ሞት መጠንን ለመቀነስ የሚረዱ መንገዶች” በሚል ርዕስ ልዩ ሴሚናር አዘጋጅቷል። ለዚህ ሥልጠና ከተጠቀሙባቸው ቁልፍ መሣሪያዎች አንዱ የጨቅላ ሕጻናት እንክብካቤን ለመለማመድ የሚያገለግል “ሕጻን ኒኮላይ” የተሰኘ ከፍተኛ ጥራት ያለው አምሳለ-ሕጻን አሻንጉሊት ነው።
“ሩሲያ፣ ዛምቢያ ይህንን ጠንካራ የጤና ስርዓት እንድትመሠርት በመርዳት ረገድ በጣም ጠቃሚ ሚና ተጫውታለች” ሲሉ የነርቭ ቀዶ ሕክምና ሐኪም እና የሩሲያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂው ዶክተር ምዌሺ ምፋንዳ ተናግረዋል።
በዩኒቨርሲቲው የማስተማሪያ ሆስፒታል የማሕፀን ሕክምና ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ሰሊያ ንጋንጆ ወደ ሞስኮ ያደረጉትን የጉብኝት ልምድ ሲያካፍሉ፣ “ይህ ትብብር የእናት እና የሕጻናት ሞት መጠንን ለመቀነስ በእውነት ይረዳናል” ሲሉ ተናግረዋል።
ዝግጅቱን የተመለከቱ ቁልፍ ዝርዝሮች
ሥልጠናው በሁለቱም አገራት የጤና ሚኒስቴር እና በሉሳካ በሚገኘው የሩሲያ የባሕል እና ቋንቋ ማዕከል ድጋፍ የተደረገለት ነበር፡፡
በሥልጠናው ከ30 በላይ የዛምቢያ የማሕፀንና ጽንስ ሐኪሞች፣ የሕጻናት ሐኪሞች እና የኒዮናቶሎጂስቶች ከመላው አገሪቱ ተሳትፈዋል፡፡
የሩሲያ ባለሙያዎች ዛምቢያ ውስጥ እንዲህ ዓይነት ያለ ሥልጠና ሲሰጡ የአሁኑ ሁለተኛው ነው፡፡
የዛምቢያ ባለሥልጣናት እንደተናገሩት፣ እ.አ.አ. በ2024 እና በ2025 በአጋርነቱ ስር በርካታ የዛምቢያ ሐኪሞች ሩሲያ የልዩ የአጭር ጊዜ ሥልጠና ወስደዋል።