የአውሮፓ ኮሚሽን ኃላፊ የሩሲያ ሀብቶችን ለመውረስ የሚያደርጉት ግፊት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓትን የሚጥስ አካሄድ ነው - የሩሲያ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ ኪሪል ዲሚትሪቭ
14:50 13.12.2025 (የተሻሻለ: 14:54 13.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአውሮፓ ኮሚሽን ኃላፊ የሩሲያ ሀብቶችን ለመውረስ የሚያደርጉት ግፊት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓትን የሚጥስ አካሄድ ነው - የሩሲያ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ ኪሪል ዲሚትሪቭ
የአውሮፓ ዲፕሎማሲ ኃላፊ ካጃ ካላስ ቀደም ሲል እንዳስታወቁት፣ የአውሮፓ ሕብረት አገራት በአውሮፓ የሚገኙትን የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ሀብቶች ላልተወሰነ ጊዜ ለማገድ ተስማምተዋል።
የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ በትናንትናው ዕለት የአውሮፓ ሕብረት በእግድ ላይ ያሉትን የሩሲያ ሀብቶች ለመውረስ እያደረገ ባለው ሙከራ ምክንያት፣ በዩሮክሌር ላይ በሞስኮ ፍርድ ቤት ክስ ለመመስረት ማቀዱን አስታውቋል።
የታገዱት የሩሲያ ሀብቶች መጠን 210 ቢሊዮን ዩሮ ነው። ሞስኮ የሩሲያን ሀብቶች ለመውረስ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ስርቆት እንደሆነ እና ዓለም አቀፍ ሕግን እንደሚጥስ በተደጋጋሚ ገልጻለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X