ከመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው በኋላ ወደ 200 የሚጠጉ የናይጄሪያ እና የአይቮሪኮስት ወታደሮች ቤኒን ውስጥ ተሰማርተዋል - የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱከመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው በኋላ ወደ 200 የሚጠጉ የናይጄሪያ እና የአይቮሪኮስት ወታደሮች ቤኒን ውስጥ ተሰማርተዋል - የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ከመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው በኋላ ወደ 200 የሚጠጉ የናይጄሪያ እና የአይቮሪኮስት ወታደሮች ቤኒን ውስጥ ተሰማርተዋል - የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.12.2025
ሰብስክራይብ

ከመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው በኋላ ወደ 200 የሚጠጉ የናይጄሪያ እና የአይቮሪኮስት ወታደሮች ቤኒን ውስጥ ተሰማርተዋል - የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አቢጃን 50 ወታደሮቿን እንደላከች የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚክ ማኅበረሰብ (ኢኮዋስ) የገለፀ ሲሆን፣ ስምሪቱ የጋና እና የሴራሊዮን ወታደሮችን እንደሚያካትት የአይቮሪኮስት የደህንነት ምንጭ አስታውቋል። ናይጄሪያ ወታደሮቿ እሁድ ዕለት ቤኒን መግባታቸውን አረጋግጣለች።

ናይጄሪያ፣ ፈረንሳይ እና ኮትዲቯር ጣልቃ በመግባት የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራውን ለማክሸፍ እና የቤኒንን ሲቪል መንግሥት በመደገፍ ረድተዋል። ቤኒን እርዳታ በጠየቀችበት ወቅት መፈንቅለ መንግሥቱ ከከሸፈ ነበር ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦሉሼጉን አድጃዲ ባካሪ ተናግረዋል።

ጥቃት አድራሾቹ ከጠዋቱ በ3:00 ሰዓት በፕሬዝዳንቱን መኖሪያ ቤት ላይ ጥቃት ቢፈፅሙም የሀገሪቱ መከላከያ ሰራዊት በፍጥነት እንዳስቆማቸው አስረድተዋል። ባካሪ አክለውም ከናይጄሪያ እና ከሌሎች የኤኮዋስ ሀገራት ድጋፍ ለማግኘት ድርድር በተጀመረበት ወቅት የቤኒን ጦር አጥቂዎቹን መመለሱን ተናግረዋል።

🪖 የናይጄሪያ አየር ሃይል በኮቶኑ ህዝብ በሚበዛበት አካባቢ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ተጠልለው የነበሩትን ጥቃት አድራሾች ከቦታው ለማባረር ተሰማርቷል። ፕሬዝዳንት ታሎን በጦር ሰፈሩ ውስጥ ብረት ለበስ የጦር ተሽከርካሪዎችን ኢላማ እንዲደረጉ እና አማፂያኑ አየር ማረፊያውን እንዳይቆጣጠሩ የአየር ድጋፍ ጠይቀዋል ሲሉ ባካሪ አስረድተዋል።

የኢኮዋስ ወታደሮች ቤኒን ውስጥ የሚኖራቸው የቆይታ ጊዜ በሚቀጥሉት ቀናት እንደሚወሰን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አመላክተዋል።

በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምስል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0