- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ቁልፍ የኃይል ቋት የመሆን ብርቱ ጥረቷ ሲቃኝ

ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ቁልፍ የኃይል ቋት የመሆን ብርቱ ጥረቷ ሲቃኝ
ሰብስክራይብ
''የኃይል ዘርፍ ለአንድ ሀገር ዕድገት ምሰሶ የሚባል ነው — ከዚህ አኳያ እንደ ሀገር የራስን ፍላጎት ሸፍኖ ወደ ቀጠናው በመላክ የበለጠ የምጣኔ ሐብት ተፅዕኖን መፍጠር የሚያስችል እጅግ በጣም ወሳኝና ለዕድገት ዘለቄታዊነት ቁልፍ ስትራተጂ የሚባል ነው '' ሲሉ በኮይሻ ሀይድሮ ፓወር የፕሮጀክቱ ምክትል ዳይሬክተር ኢንጂነር አባይነህ ጌትነት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ሁለት አንኳር ጉዳዮችን በምንቃኝበት ፕሮግራማችን፣ በክፍል አንድ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይልን በማምረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ከመጣው የኃይል ፍላጎት ባለፈ በምትገኝበት ቀጠና ቁልፍ የኃይል ቋት የመሆን ብርቱ ጥረቷን በተመለከተ በኮይሻ ሀይድሮ ፓወር የፕሮጀክቱ ምክትል ዳይሬክተር ኢንጂነር አባይነህ ጌትነትን በእንግድነት ጋብዘንላችኃል። በሁለተኛው ክፍል ደግሞ በሪቨርስ ኢንጂነሪንግ ዘርፍ በአፍሪካ አህጉር ደረጃ የትብብር መዋቅር መፈጠር ስለሚቻሉባቸው ጉዳዮች በባዮ ኤንድ ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ተቋም የሪቨርስ ኢንጂነሪግ ባለሙያው ክንፈ ገብርኤል ከበደ ምልከታቸውን ያጋሩናል።
ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0