- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የሐይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴቶች ሚና ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል

የሐይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴቶች ሚና ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል
ሰብስክራይብ
“የመጀመሪያው ትልቁ ነገር የሰውን ልጅ ክብር ማሳወቅ ነው። የሰው ልጅ ክብር፣ አንዱ ጉልበት ስላለው ሌላውን ጉልበት የሌለውን የማጥቃት መብት እንዳለው ተደርጎ የሚቆጠርበት አለመሆኑን፣ ሰውን ማክበርን ፈጣሪን መፍራትን፣ ህግን መጠበቅን በተለይ ደግሞ አጥቂነትን፣ የአጥቂነት ባህሪን በተቻለ መጠን አውግዞ በማስተማር የሀይማኖት ተቋማት ትልቅ ድርሻ አላቸው።” ሲሉ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የስነመለኮት መምህር የሆኑት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጾታን መሰረት ስላደረገ ጥቃት እንዲሁም በመንግስት እና በሃይማኖት ተቋሟት በኩል መደረግ ስለሚገባቸው የተለያዩ ተግባራት በሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የሴቶች መብት ጥበቃና ምላሽ መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ዘካሪያስ ደሳለኝን፣ የህግ ባለሙያ እና የሴቶችን አቅም ማጎልበት ባልሙያ የሆኑትን ወ/ሮ ቤተልሄም ድጉን እንዲሁም በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የስነመለኮት መምህር የሆኑት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ያነጋገርናቸው ሲሆን፤ ቻይና በኤሌክትሪክ መኪኖች ሽያጭ ላይ ያወጣቸው ጥብቅ ፖሊሲን ተከትሎ በኢትዮጵያ ላይ ሊፈጥር የሚችለውን ጫና በኤሌክትሪክ መኪኖች ዙሪያ በማማከር ከሚታወቁት ከአቶ ብሩክ አወቀ ጋር ያደረግነው ውይይት በሁለተኛው የመሰናዶኣችን ክፍል ተካትቷል፡፡

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ :

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0