ፑቲን ከቬንዙዌላው ፕሬዝዳንት ማዱሮ ጋር ተወያዩ
18:47 11.12.2025 (የተሻሻለ: 18:54 11.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፑቲን ከቬንዙዌላው ፕሬዝዳንት ማዱሮ ጋር ተወያዩ
ከቬንዙዌላ ሕዝብ ጋር ያላቸውን አጋርነት እና እያየለ በመጣው የውጭ ጫና ወቅት፣ የማዱሮ መንግሥት ብሔራዊ ጥቅምን እና ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ የተከተለውን አካሄድ እንደሚደግፉ ገልፀዋል፡፡
የአገራት መሪዎቹ፣ በተጨማሪም በሕዳር ወር ገቢራዊ በተደረገው ስትራቴጂካዊ አጋርነት እና የትብብር ስምምነት ጋር በተጣጣመ መልኩ ወዳጃዊ የሩሲያ እና የቬኔዙዌላን ግንኙነትን በተመለከተም ሐሳብ ተለዋውጠዋል።
በንግድና ኢኮኖሚ፣ በኢነርጂ፣ በፋይናንስ፣ በባሕልና ሰብአዊ ዕርዳታና ሌሎች ዘርፎች ላይ የጋራ ፕሮጀክቶችን በተከታታይ ተግባራዊ ለማድረግ የጋራ ቁርጠኝነታቸውንም አረጋግጠዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X