የኢትዮጵያን ጨቅላ ሕጻናትን ጤና ያሻሽላል የተባለለት ገመድ አልባ ተለባሽ መከታተያ ስርዓት ይፋ ሆነ
18:37 11.12.2025 (የተሻሻለ: 18:54 11.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያን ጨቅላ ሕጻናትን ጤና ያሻሽላል የተባለለት ገመድ አልባ ተለባሽ መከታተያ ስርዓት ይፋ ሆነ
ይህ አዲስ፣ ለስላሳ፣ ሁሉ አቀፍና የሚለበስ ፈጠራ በደረት ላይ የሚለጠፍ ሽፋን እና በግንባር ላይ የሚለጠፍ የደም ምት መልኪያ (ፐልስኦክሲሜትሪ) ያካተተ ሲሆን፣ መረጃዎችን በቅጽበት ወደ ስማርትፎን መተግበሪያ ያስተላልፋል።
የልብ ምት፣ የአተነፋፈስ ፍጥነት፣ የሰውነት ሙቀት፣ የደም ግፊት፣ ኤሌክትሮካርዲዮግራም እና በደም ውስጥ ያለው የኦክስጂን መጠን የመሳሰሉ ጠቃሚ ክሊኒካዊ መለኪያዎችን ለክቶ ይመዘግባል፡፡
ያልተለመዱ ንባቦችን በፍጥነት በማሳወቅም የጨቅላ ሕጻናትን የሞት ምጣኔ በእጅጉ ሊቀንስ ይችላል፡፡
በጥናታዊ ሙከራው ወቅት ከተሳተፉት ወላጆች 84 በመቶ የሚሆኑት ቴክኖሎጂውን በቤታቸው ለመጠቀም ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸው ተዘግቧል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/