- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ትምህርትና ሉዓላዊነት ፡- የአፍሪካ የመምህራን ሥልጠናን ከቅኝ ግዛት ጥላ ነጻ መውጣት

ትምህርትና ሉዓላዊነት ፡- የአፍሪካ የመምህራን ሥልጠናን ከቅኝ ግዛት ጥላ ነጻ መውጣት
ሰብስክራይብ
“ቀጥታ የውጭውን ዓለም የሥርዓተ ትምህርት ከኢትዮጵያውያን ህይወት ጋር ብዙም ግንኙነት የሌለው፣ ልጆቹን ትራንስፎርም የማያደርግ፣ አካባቢውን የማይለውጥ፣ አካባቢውን ያልተገነዘበ ሥርዓተ ትምህርት ታመጣና [...] ኢትዮጵያ አምጥተህ ስታስቀምጠው አይገጣጠምም፡፡” በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ እና የትምህርት ኮሌጅ የሳይንስ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር እና በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አማካሪ ምክር ቤት አባል ሰለሞን በላይ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት ላይ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ እና የትምህርት ኮሌጅ የሳይንስ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር እንዲሁም በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አማካሪ ምክር ቤት አባለ ከሆኑት ከሰለሞን በላይ (ዶ/ር) ጋር የመምህራን ትምህርትን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ማድረግ ምን ማለት እንደሆነ፤ ይህም የአፍሪካን ጥበብ፣ ባህል እና ማንነት ወደ ትምህርት ዋና ማዕከል መመለስ እንዴት እንደሚቻል፤ እንዲሁም አፍሪካ የትምህርት ሥርዓቷን የራሷን እውነታዎች እንዲያንፀባርቁ አድርጋ ዳግም እንዴት ልትቀርጽ ትችላለች? የሚሉና ተያያዥ ጉዳዮች የተንሱበትን ይህን መሰናዶ ይከታተሉ።

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0