ካምቦዲያ ከታይላንድ ጋር ባላት የድንበር ውጥረት ዙሪያ ለዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ማስረጃ ለማቅረብ እያዘጋጀች መሆኑ ተነገረ

ካምቦዲያ ከታይላንድ ጋር ባላት የድንበር ውጥረት ዙሪያ ለዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ማስረጃ ለማቅረብ እያዘጋጀች መሆኑ ተነገረ
የግጭቱ የቅርብ ጊዜ ሁነቶች፦
የካምቦዲያ ብሔራዊ መከላከያ ሚኒስቴር የታይላንድ ወታደሮች በባንቴይ ሜያንቼ ግዛት የመኖሪያ አካባቢዎች መርዛማ ጋዝ ተጠቅመዋል ሲል ከሷል።
አሜሪካ አስቸኳይ የተኩስ ማቆም እንዲደረግ ጥሪ ያቀረበች ሲሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፤ ዋሽንግተን በደረሱ ጉዳቶች ላይ ያላትን ስጋት ገልጸው ወደ ጥቅምት 16ቱ የኩዋላ ላምፑር የሰላም ስምምነቶች እንዲመለሱ ጠይቀዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ጣልቃ በመግባት ግጭቱን ለማስቆም የስልክ ጥሪ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።
ካምቦዲያ ጦሯ በሁሉም አወዛጋቢ የድንበር አካባቢዎች የመልሶ ማጥቃት እንዲፈጽም ያዘዘች ሲሆን፤ የካምቦዲያ ሕዝባዊ ፓርቲ መሪ ሁን ሴን ታይላንድ 11 የካምቦዲያ ቦታዎችን ለመያዝ እንዳሰቡ ተናግረዋል።
የታይላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር አኑቲን ቻርንቪራኩል ፎኖም ፔን ለድርድር ከማንም ጋር ግንኙነት እንዳልተፈጠረ እና ወታደሮች ሁኔታውን እየተቆጣጠሩ ነው ብለዋል።
ካምቦዲያ ከባድ የደህንነት ስጋቶች በማንሳት የአትሌቶቿን ታይላንድ ከሚካሄደው የደቡብ ምስራቅ እስያ ጨዋታዎች አስወጥታለች።
በካምቦዲያ ቢያንስ 9 ንፁሃን ዜጎች ሲገደሉ ወደ 20 የሚጠጉ ቆስለዋል ሲል አልጀዚራ የአካባቢውን ባለስልጣናት ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፤ በታይላንድ ደግሞ 4 ወታደሮች ሲገደሉ በቅርብ ጊዜ የደረሱትን ጨምሮ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ቆስለዋል።
የታይላንድ ባለሥልጣናት ሊፈፀሙ የሚችሉ የድሮን ጥቃቶችን ለመቀነስ ማክሰኞ ምሽት በድንበር አካባቢዎች መብራቶችን አጥፍተዋል።
የታይላንድ ኤፍ-16 ተዋጊ ጄቶች በሳምራኦንግ የሚገኘውን የካምቦዲያ ወታደራዊ ቦታ በመምታት የቢኤም-21 ሮኬት ማከማቻ እና ከባድ መሳሪያዎችን አውድመዋል።
የካምቦዲያ ባለሥልጣናት ከታይላንድ ጋር በተባባሰው ግጭት ምክንያት ከ100 ሺ በላይ የድንበር ግዛት ነዋሪዎች እንደሸሹ ዘግበዋል። ታይላንድ ወደ 400 ሺህ የሚጠጉ ሰዎችን ያስወጣች ሲሆን 125 ሺህ የሚሆኑት በድንበር አቅራቢያ በሚገኙ ጊዜያዊ መጠለያዎች ውስጥ ይገኛሉ።
አንድ የካምቦዲያ ቢኤም-21 ግራድ ሮኬት በሱሪን ግዛት በፋኖም ዶንግ ራክ ሆስፒታል አቅራቢያ በማረፉ፤ የህክምና ባለሙያዎች እና ታካሚዎች በአደጋ ጊዜ መጠለያ እንዲገቡ ሆኗል።
ከፍተኛ የንግድ ታሪፍ ማስፈራሪያዎች ታይላንድ ከካምቦዲያ ጋር የሰላም ንግግሮችን እንድታደርግ ግፊት አያደርጉም፤ ፎኖም ፔን መጀመሪያ የግጭቱን ማብረጂያ እርምጃ መውሰድ አለባት ሲሉ የታይላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲሃሳክ ፉንግኬትኬኦ ተናግረዋል።
ከካምቦዲያ ጋር እየተባባሰ በመጣው ግጭት ሳቢያ የታይላንድ ባሕር ኃይል በአየር ኃይል ድጋፍ "ትራት ሰፕረስ ፎስ" የሚል ኦፕሬሽን እንደጀመረ በትራት ግዛት የሚገኘው የድንበር መከላከያ ኃይሎች ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X