የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የፍሳሽ ማስወገጃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀመረ
16:21 10.12.2025 (የተሻሻለ: 16:24 10.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የፍሳሽ ማስወገጃ ፕሮጀክት ግንባታ አስጀመረ
ፕሮጀክቱ በ2.24 ቢሊዮን ብር በመቀሌ ከተማ የሚገነባ መሆኑን የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ አስታውቀዋል፡፡
ወጪው ከዓለም አቀፍ ተቋም በተገኘ ብድር እንደሚሸፈን እና በአስራ ስምንት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሩ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፐሬዝዳንት ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ ጋር በመሆን ለግንባታው የመሠረተ ድንጋይ ማስቀመጣቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አጋርተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X