የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጥር 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ጂዛን ከተማ ቀጥተኛ በረራ እንደሚጀምር ተገለፀ
14:16 10.12.2025 (የተሻሻለ: 14:24 10.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጥር 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ጂዛን ከተማ ቀጥተኛ በረራ እንደሚጀምር ተገለፀ
አየር መንገዱ በደቡብ ምዕራብ ሳዑዲ አረቢያ ወደምትገኘው ወሳኝ የቀይ ባሕር ወደብ ከተማ በሳምንት አራት ቀን አዲስ የመንገደኞች አገልግሎት እንደሚጀመር ዋና ሥራ አስፈፃሚው መስፍን ጣሰው አስታውቀዋል።
“በአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅ እና ባሻገር ባሉ ሀገራት መካከል የንግድ፣ የቱሪዝም እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን ለማሳደግ ያለመ ነው” ሲሉ ገልፀዋል።
ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳዑዲ አረቢያ የበረራ መዳረሻዎቹን ወደ አምስት አሳድጓል፡፡
አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት በሳምንት ከ40 በላይ በረራዎችን ወደ ሳዑዲ አረቢያ እንደሚያደረግ የተቋሙ መረጃ ያመላክታል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X