ጊፋታ በማይዳሰስ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስነት በዩኔስኮ ተመዘገበ
12:09 10.12.2025 (የተሻሻለ: 15:14 10.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጊፋታ በማይዳሰስ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስነት በዩኔስኮ ተመዘገበ
የወላይታ ሕዝብ ዘመን መለወጫ ፌስቲቫል ዩኔስኮ ያስቀመጣቸውን አምስት መመዘኛዎች አሟልቶ በመገኘቱ ለምዝገባ መብቃቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ፌስቲቫሉ የተመዘገበው የተባበሩት መንግስታት ትምህርት፣ ሳይንስና ባሕል ድርጅት በህንድ ኒው ዴሊሂ ከተማ እያካሄደ በሚገኘው 2ዐኛው የማይዳሰስ ባሕላዊ ቅርስ ጥበቃ የመንግሥታት ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
ጊፋታን በማይዳሰስ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ያስቻሉት መገለጫዎች፦
አካታች ማህበራዊ መስተጋብር፣
ከትውልድ ትውልድ መሸጋገር በመቻሉ፣
አንድነት፣ ሰላም እና አብሮነትን ስለሚያስተጋባ፣
ቅርሱ በሀገሪቱ ብሔራዊ ምዝገባ ውስጥ የተካተተ መሆኑ፡፡
ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም 6 የማይዳሰሱ ቅርሶችን በዩኔስኮ ማስመዝገቧ ይታወሳል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


