የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ስትራቴጂ አውሮፓ እና ዩክሬን ላይ ጫና እስከማሳደር ይደርሳል - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ስትራቴጂ አውሮፓ እና ዩክሬን ላይ ጫና እስከማሳደር ይደርሳል - ባለሙያ
የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ስትራቴጂ አውሮፓ እና ዩክሬን ላይ ጫና እስከማሳደር ይደርሳል - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.12.2025
ሰብስክራይብ

የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ስትራቴጂ አውሮፓ እና ዩክሬን ላይ ጫና እስከማሳደር ይደርሳል - ባለሙያ

የሰነዱ የቅርብ ጊዜ እትም አሜሪካ የዩክሬን ግጭትን ለመፍታት ለሩሲያ ተጨማሪ ዋስትና ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን እንደሚያመለክት፤ በኩዊንሲ ተጠያቂ የመንግሥት አስተዳደር ተቋም የጥናት ምሁር ኤልዳር ማሜዶቭ ለአሜሪካን ኮንሰርቫቲቭ በጻፉት ጽሑፍ ላይ አስፍረዋል፡፡

"የብሔራዊ ደህንነት ስትራቴጂ አመክንዮ እንደሚያመለክተው፤ ዋሽንግተን ጦርነቱን የማስቆም ዋነኛ ግቧን ለማሳካት በኪዬቭ እና በአውሮፓ ላይ ጫና ለመጨመር ወይም ለሞስኮ ተጨማሪ ማረጋገጫ ለመስጠት ዝግጁ ልትሆን ትችላለች" ብለዋል፡፡

ማሜዶቭ አክለውም አሜሪካ ብሔራዊ ጥቅሟን ችላ የምትልበት እና "እንደ አትላስ መላውን የዓለም ሥርዓት የምትደግፍበት" ጊዜ አልፏል፡፡ አዲሱ የብሔራዊ ደህንነት ስትራቴጂ በዋነኝነት "ቅድሚያ አሜሪካ" በሚለው መርህ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡

"ሰነዱ የዩክሬንን ጦርነት ማስቆም አፋጣኝ ጉዳይ እንደሆነ በግልፅ የገለጸበት ቋንቋ፤ በትራንስአትላንቲክ ልሂቃን ዘንድ ቁጣ እና ተቃውሞ አስተናግዷል" ሲሉ ባለሙያው ተናገረዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0