የአውሮፓ ኅብረት ሩሲያ ትሸነፋለች በሚለው ጭፍን ፖለቲካ አሁንም ቀጥሏል - ሰርጌ ላቭሮቭ
10:45 10.12.2025 (የተሻሻለ: 10:54 10.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአውሮፓ ኅብረት ሩሲያ ትሸነፋለች በሚለው ጭፍን ፖለቲካ አሁንም ቀጥሏል - ሰርጌ ላቭሮቭ
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሩሲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ያደረጓቸው ተጨማሪ መግለጫዎች፦
ሩሲያ ከአውሮፓ ጋር ጦርነት የመጀመር ፍላጎትም ሆነ ሃሳብ የላትም፡፡
ትራምፕ በሩሲያ ላይ ማዕቀቦችን የማንሳት ሳይሆን የመጨመር ፍላጎት ነው ያላቸው፡፡
ሩሲያ እና አሜሪካ በዩክሬን ያለውን ሁኔታ ለመፍታት ትብብራቸውን ለመቀጠል ተስማምተዋል።
ሩሲያ ትራምፕ በዩክሬን ጉዳይ ዙሪያ የመወያየት ፍላጎታቸውን ታደንቃለች።
ሩሲያ በዩክሬን ውስጥ ለሚደረጉ የውጭ ወታደራዊ ጦር ኃይሎች ስምሪት ምላሽ ትሰጣለች፤ ለዚህ ዝግጅት እያደረገች ነው።
ሩሲያ ለምዕራቡ ዓለም የንብረት ወረሳ ምላሽ ትሰጣለች።
የሩሲያን ጥቅም ለመጠበቅ ያለመው ገለልተኛ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለክለሳ አይቀርብም።
ሩሲያ የኩርስክ ክልልን ከዩክሬን ነፃ ለማውጣት ላደረገችው የአጋርነት ድጋፍ ሰሜን ኮሪያን ከልብ ታመሰግናለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X