- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

አማራጭ ሀብት ለአፍሪካ ዕድገት፡ ከባህላዊ የኢንቨስትመንት መንገዶች ባሻገር

አማራጭ ሀብት ለአፍሪካ ዕድገት፡ ከባህላዊ የኢንቨስትመንት መንገዶች ባሻገር
ሰብስክራይብ
“የአማራጭ ሀብቶች ፣ ለምሳሌ የሰው ካፒታል መረጃ ጠቋሚ ምርታማነት፣ የህዝቡ መጠን እና የኢኮኖሚዎ ስፋት—ተቋማዊ ሁኔታዎችንሊቀይሩ/ሊያስተካክሉ ይችላሉ። ስለዚህ፣ አማራጭ ሀብቶች ልክ እንደ ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት በተመሳሳይ መንገድ ተጽዕኖ አያድርባቸውም፡፡” ሲሉ የማኔጅመንትና ኢኮኖሚክስ አማካሪ ሳታ አብርሃም (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት በአማራጭ ሀብት ላይ ከሚሰሩ ቀደምት ተመራማሪዎች አንዱ ከሆኑት ሳታ አብርሃም (ዶ/ር) ጋር በመሆን ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ወስጥ የግል ሀብት ፣ ቬንቸር ካፒታል ፣ መሰረተ-ልማት ፣ እና ቋሚ ንብረቶች ኢንቨስትመንት ዙሪያ ያለውን ለውጥ እና እውነታ የምንዳስስ ሲሆን፤ በሁለተኛው የዝግጅታችን ክፍል ደግሞ በመጀመሪያው የአፍሪካ ኅብረት የዲጂታል ግብርና ጉባኤ ላይ ተገኝተን በአፍሪካ ውስጥ በግብርና ሥራ ፈጣራ ላይ ከተሰማሩት ከኢንግሪድ ኤፓዛኝ (ዶ/ር) ፣ ፑሪቲ ኤኮህ-ኦዴቺኩ እና ባላቂስ ሰላውዲን ኢብራሂም ጋር ስለ ዲጂታል ግብርና ያደረግነው ውይይት ተካትቷል፡፡

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0