- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የማካካሻ ፍትህ ፦ ለአፍሪካ ለምን አስፈላጊና ወሳኝ ጥያቄ ሆነ ?

የማካካሻ ፍትህ ፦ ለአፍሪካ ለምን አስፈላጊና ወሳኝ ጥያቄ ሆነ ?
ሰብስክራይብ
“የቅኝ ግዛት ካሳ ጉዳይ ማንሳት ከታሪካዊ እይታ አንጻር ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካዊና ከሥነ-ልቦናዊ እይታ አንጻርም ጭምር በጣም አስፈላጊ ነው። ይህም አሁን ያለው የምዕራቡ ዓለም ትውልድ እንዲሁም አሁን በአፍሪካ እና በሌሎች በዓለም ዙሪያ በሚገኙ የቅኝ ግዛት ሥር በነበሩ አገሮች የሚኖሩት ትውልዶች በእነዚህ አካባቢዎች ጭቆና፣ ብዝበዛ እና አሰቃቂ የቅኝ ግዛት አገዛዝ እንደነበረ ማወቅ አለባቸው።” ሲሉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዳዊት መዝገበ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዳዊት መዝገበ፣ የቅኝ ግዛት ካሳ ለአፍሪካ ክብር፣ ሉዓላዊነትና ልማት አስፈላጊ የሆነበትን ምክንያት እንዲሁም በሁለተኛው የዝግጅታችን ክፍል ደግሞ በናይጄሪያ ሴኪውሪቲስ እና ኤክስቼንጅ ኮሚሽን የሕግ እና ክስ ጉዳዮች መምሪያ ም/ዳይሬክተርና ኃላፊ ፍራንሲስ ኡዞማ ኦካፎር (ዶ/ር) ፣ በናይጄሪያ ሴኪውሪቲስ እና ኤክስቼንጅ ኮሚሽን የሕግ መምሪያ ዳይሬክተር ኔስተር ኢኬአጉ ፣ እንዲሁም በሴድረስ ግሩፕ አፍሪካ ሥራ አስፈፃሚ ዳይሬክተር ዴሌ አኪንጆን በአፍሪካ አህጉር ውስጥ የካፒታል ገበያ አስፈላጊነትን አስመልክቶ ያደረግነው ውይይት ተካትቷል፡፡

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0