- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

የባዮ ኢኮኖሚ ለውጥ በአፍሪካ፡- ከአህጉሪቷ እስከ ብሪክስ ማዕቀፍ የተዘረጋው ትብብር

የባዮ ኢኮኖሚ ለውጥ በአፍሪካ፡- ከአህጉሪቷ እስከ ብሪክስ ማዕቀፍ የተዘረጋው ትብብር
ሰብስክራይብ
''ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ያሏት የኢንዱስትሪያል ፓርኮች ለሌሎቹ ሀገራት ምሳሌ መሆን የሚችሉ ናቸው — የብሪክስ ማዕቀፍ በአህጉሪቱ ያሉ ሀገራት በዘርፉ የላቀ ደረጃ እንዲደርሱ ትልቅ ዕድልን አመቻችቷል'' ሲሉ በባዮ ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ተቋም የኢንዱስትሪያል ባዮ ቴክኖሎጂ ዳይሮክቶሬት ስር ተመራማሪና የቡድን መሪ ፍሬው ታፈሰ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ሁለት ጉዳዮችን በምንዳስስበት የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም፣ በክፍል አንድ የአፍሪካ ሀገራት በባዮ ኢኮኖሚ ዘርፍ እንዴት በብሪክስ ማዕቀፍ ስር ራሳቸውን ያሥተሳስሩ ስንል በባዮ ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ተቋም የኢንዱስትሪያል ባዮ ቴክኖሎጂ ዳይሮክቶሬት ስር ተመራማሪና የቡድን መሪ ፍሬው ታፈሰ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተናል። በሁለተኛው ክፍልም የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ከምዕራባዊያን የእርዳታ ድጋፎች ተላቅቀው ውስጣዊ የፋይናንስ አቅማቸውን መገንባት በሚችሉበት ጉዳይ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ ፣ የኢትዮጵያ አረጋዊያንና ጡረተኞች ብሔራዊ ማኅበር ም/ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጌታቸው ክፍሉ እና በሄልፕ ኤጅ ኢትዮጵያ ሲኒየር ፕሮግራም አድቫይዘር ሶፊያ መሃመድ ጋር ቃኝተናል።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0