“የግብርና መድህን በአገራችን ውስጥ የሚፈለገውን ያህል አላደገም፡፡ ከአጠቃላይ ኢንዱስትሪው ከሚሰጠው የመድህን ሽፋን የግብርና ኢንሹራንስ ስናየው ከ 1 በመቶ አይዘልም፡፡ እስካሁን የተሰራው፡፡ እሱም ቢሆን ደግሞ በአብዛኛው ኮሜርሻል ፋርም ጋር የሚያያዝ ነው፡፡” ሲሉ የኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ባለሙያዎች ማህበር ምክትል ፕሬዝደንት እንዲሁም የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አክሲዮን ማኅበር የስትራቴጂ እና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቅሩ ፀጋዬ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ባለ ሁለት ክፍል ዝግጅት፣ በመጀመሪያው ክፍል በኢትዮጵያ ውስጥ የግብርና መድህን ያለበትን ደረጃ እና አገልግሎቱን ተደራሽ በማድረግ ረገድ እያጋጠሙ ስላሉ የተለያዩ ተግዳሮቶች የኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ባለሙያዎች ማህበር ም/ፕሬዝደንት እንዲሁም የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አክሲዮን ማኅበር የስትራቴጂ እና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቅሩ ፀጋዬ ጋር የተወያየን ሲሆን፤ የሁለተኛውን የግብርና ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር ፕሮጀክት በይፋ የማስጀመር መርሀ-ግብር አስመልክቶ ያዘጋጀነው መሰናዶም ተካትቷል፡፡
ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple Podcasts – Spotify – Deezer – Afripods – Podcast Addict – Pocket Casts – CastBox
ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple Podcasts – Spotify – Deezer – Afripods – Podcast Addict – Pocket Casts – CastBox

