ኬንያ በሀገሪቱ ውስጥ ባለው የእንግሊዝ ጦር ማሠልጠኛ ክፍል ላይ ያደረገችው ቁጥጥር አፍሪካውያን ይበልጥ በጉዳዩ እንዲገፉ ሊያደርግ ይገባል - መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ኃላፊ

ሰብስክራይብ

ኬንያ በሀገሪቱ ውስጥ ባለው የእንግሊዝ ጦር ማሠልጠኛ ክፍል ላይ ያደረገችው ቁጥጥር አፍሪካውያን ይበልጥ በጉዳዩ እንዲገፉ ሊያደርግ ይገባል - መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ኃላፊ

የኬንያ ፓርላማ የምርመራ ኮሚቴ በሀገሪቱ የእንግሊዝ ጦር ማሰልጠኛ ክፍል ላይ ያደረገው ምርመራ፤ እንደ ጄምስ ምዋንጊ ገለፃ በአፍሪካ ምድር ያሉ የውጭ ወታደራዊ ኃይሎች አሠራር ላይ በጣም የዘገየ እርምጃ ነው።

“ፓርላማው የእንግሊዝ ጦር የሥልጠና እንቅስቃሴዎችን ለመቆጣጠር መወሰኑ ትልቅ እርምጃ ነው፡፡ ሌሎች የአፍሪካ ፓርላማዎች አብዛኞቹን እነዚህን የጦር ሠፈሮች ተነሳሽነት ወስደው እንዲቆጣጠሩ የሚያነቃቃ ጥሪ ነው” ሲሉ የአፍሪካ የእርምትና የመከላከል እርምጃዎች ማዕከል መስራች ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ምዋንጊ ለብዙ አሥርተ ዓመታት የተፈጸሙ ጥፋቶችን አጉልተው አንስተዋል፡፡ ወሲባዊ ጥቃት፣ የአካባቢ ብክለት እና በተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያደርሱ ጉዳቶችን ለአብነት ጠቅሰዋል።

የታገደውን ነጭ ፎስፈረስ “አርብቶ አደሮች… ሰዎች እና እፅዋት ባሉበት ስሱ ሥነ ምህዳር” መጠቀምን አውግዘው፤ “የአፈራችን… የእፅዋታችን… የሕይወታችን እና የውሃ አካሎቻችን መበከል” ሲሉ ገልጸውታል።

ፓርላማው ያገኛቸው ግኝቶች አስቸኳይ እርምጃ ሊያስከትሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። አደገኛ የሥልጠና ቅሪቶች፤ "ሳይፈነዱ በመሬት ውስጥ ተቀብረው የተተዉ አደገኛ መሣሪያዎች" በሰዎችና በእንስሳት ላይ ሞት አስከትለዋል።

ተጠያቂነት ዓለም አቀፍ የሥልጣን ተለዋዋጭነትንም ማካተት እንዳለበት ምዋንጊ አጽንኦት ሰጥተዋል። የውጭ ጦር ሠራዊቶች በአፍሪካ በነጻ ሥልጠና ከሰጡ፤ “የኬንያ መንግሥትም በእንግሊዝ የሥልጠና ካምፕ ሊኖረው ይገባል” ሲሉ ሞግተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0