- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የዘረመል ንቅለ ተከላ እና ጂኦፖለቲካ፡ የኢትዮጵያን የወደፊት ሁኔታ የሚቀርጹ ሁለቱ ኃይሎች

የዘረመል ንቅለ ተከላ እና ጂኦፖለቲካ፡ የኢትዮጵያን የወደፊት ሁኔታ የሚቀርጹ ሁለቱ ኃይሎች
ሰብስክራይብ
“[ምዕራቡ ዓለም] ወጥመድ ውስጥ ለማስግባት ይሞክራሉ፣ ምክንያቱም በገንዘብ በሚረዱበት ጊዜ ሁሉ የራሳቸውን መስፈርት ያስቀምጣሉ። የአንተ ፍላጎት በእነሱ ቅድሚያ የሚሰጠው አይደለም።[...] አንተ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ነገሮች የትኞቹ እንደሆኑ መወሰን አለብህ። ለእነዚያም ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ዘርፎች ከሀገር ውስጥ ገንዘብ እንዲገኝ ማድረግ ይገባል።” ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ጄኔቲክስ ተባባሪ ፕሮፌሰር ደረጀ በየነ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ የዘረመል ንቅለተከላ (የጂኖም ኤዲቲንግ) የአፍሪካን የምግብ ስርዓት፣ ሳይንሳዊ ሉዓላዊነት እና የመቋቋም አቅም እንዴት እየለወጡ እንደሆነ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ጄኔቲክስ ተባባሪ ፕሮፌሰር ከሆኑት ከ ደረጀ በየነ (ዶ/ር) ጋር የተወያየን ሲሆን፤ ወደ አፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ተሻግረን የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በቅርቡ ባደረጉት ንግግር ዙሪያ፣ በቀይ ባህር ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ዙሪያ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፈር በድሩ(ዶ/ር) እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ፕሮፌሰር ብሩክ ኃይሉ የሰጡንን ትንታኔ አካትተናል፡፡

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0