- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የባህል ኃይል፡ ከጋና አሳንቴ ቅርስ እስከ የአፍሪካ ሴቶች የፍትህ ትግል እና የምግብ ሉዓላዊነት

የባህል ኃይል፡ ከጋና አሳንቴ ቅርስ እስከ የአፍሪካ ሴቶች የፍትህ ትግል እና የምግብ ሉዓላዊነት
ሰብስክራይብ

“ብዙ ሰው እንደሚያስበው ባህል የአኗኗር ዘይቤ አደለም፤ ባህል ራሱ ሕይወት ነው። ሁሉም ህይወት ባህል ነው። ባህል ማንነትህን ይገልጻል። ባህል አንተ ማን እንደሆንክ ያደርግሃል። ባህል ህይወት ነው ስል፣ ባህልን እንወልዳለን። ባህልን እናወራለን። በባህል እንኖራለን። በባህል እንተኛለን። በባህል እንንቀሳቀሳለን። በባህል እንሄዳለን። እና ባህልን እንሰራለን። ስለ ህይወት ያለው ነገር ሁሉ ባህል ነው። ባህልህን የሚቆጣጠር ሁሉ ሀብትህን ይቆጣጠራል።” ሲሉ የቴስት ኦፍ አፍሪካ ተባባሪ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቴንጎል ኬፕለማኒ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በዚህኛው ሦስት ጉዳዮችን በሚዳስሰው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት ፣ በክፍል አንድ የቴስት ኦፍ አፍሪካ ተባባሪ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሆኑት ከቴንጎል ኬፕለማኒ ጋር በመሆን የአፍሪካ ባህላዊ እሴት እና ጥበብን እንዴት መልሶ ማምጣት እንደሚቻል፤ በክፍል ሁለት በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር የይሶን አርካዲዮ ትርክቶችን ለአፍሪካ ሴቶች ፍትህ ለማምጣት ስለመጠቀም፤ እንዲሁም በክፍል ሦስት በሌሴቶ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ውስጥ ባለሙያ የሆኑት ከሲትዚ ፖርታስ የአፍሪካን የምግብ ሉዓላዊነት ስለመጠበቅ ግንዛቤያቸውን ያጋራሉ።

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0