የናይጄሪያ የጸጥታ ኃይሎች ታፍነው የተወሰዱ 100 ተማሪዎችን ማስለቀቃቸው ተዘገበ
18:57 08.12.2025 (የተሻሻለ: 19:04 08.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ የጸጥታ ኃይሎች ታፍነው የተወሰዱ 100 ተማሪዎችን ማስለቀቃቸው ተዘገበ
ልጆቹ ህዳር 14 ቀን በናይጀር ግዛት ፓፒሪ ከሚገኘው የሴንት ሜሪ የግል ካቶሊክ ትምህርት ቤት በታጣቂዎች ታፍነው ከተወሰዱት 303 ተማሪዎች እና 12 አስተማሪዎች መካከል መሆናቸውን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡
ለሦስት ሰዓት ያህል በፈጀው የጠዋት ድንገተኛ ጥቃት ወቅት ቢያንስ ሃምሳ ተማሪዎች ማምለጥ ችለዋል። ሆኖም 265 ተጎጂዎች እንደጠፉ በመዘገቡ የብሔራዊ ደህንነት ምላሽ እንደተሰጠ ሪፖርቶች አመልክተዋል።
የፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ መንግሥት በበርካታ ግዛቶች የምድር እና አየር ኃይሎችን በማሰማራት፤ በድንበር አካባቢዎች የፀጥታ ጥበቃ እንዲጠናከር እንዲሁም በናይጀር ግዛት የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ለጊዜው እንዲዘጉ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ታጋቾቹ የተለቀቁት በክልሉ አሁንም የጥቃት ድርጊቶች በቀጠሉበት ወቅት ነው። በቅርቡ በሺሮሮ የአካባቢያዊ መንግሥት 24 አርሶ አደሮች ታፍነው ሲወሰዱ፤ በአንድ ማየት የተሳናቸው ነዋሪ ላይ አሰቃቂ ጥቃት ተፈፅሟል።
ፖሊስ የቀሩትን ታጋቾች ለማዳን የሚደረገው ጥረት እንደቀጠለ አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X