የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ወንዶች ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል እንዲንቀሳቀሱ አሳሰቡ

© telegram sputnik_ethiopiaየደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ወንዶች ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል እንዲንቀሳቀሱ አሳሰቡ
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ወንዶች ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል እንዲንቀሳቀሱ አሳሰቡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.12.2025
ሰብስክራይብ

የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ወንዶች ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል እንዲንቀሳቀሱ አሳሰቡ

ሲሪል ራማፎሳ ፆታዊ ጥቃት እና የሴቶች ግድያ ወንጀልን ለመከላከል ጠንካራ ብሔራዊ ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል። ጥሪው መንግሥት ፆታዊ ጥቃቶችን እና የሴቶች ግድያን ሀገር አቀፍ አደጋ አድርጎ መፈረጁን ተከትሎ የመጣ ነው።

"ከ18 ዓመት በላይ የሆናቸው ከ35 በመቶ በላይ ደቡብ አፍሪካውያን ሴቶች አካላዊ ወይም ወሲባዊ ጥቃት እንደሚደርስባቸው" የሚገልጸውን ብሔራዊ የፆታዊ ጥቃት የ2022 ጥናት በመጥቀስ፤ ጾታዊ ጥቃት ምናልባትም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ "የበለጠ አጥፊ" እንደሆነ አስጠንቅቀዋል።

ይህ ወንጀል በስጋትነት መፈረጁ ፈጣን የሀብት ምደባ፣ የተስፋፉ መጠለያዎች እና የምክር አገልግሎቶች እንዲሁም የማህበራዊ ልማት፣ የፍትሕ፣ የጤና እና የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ አገልግሎትን ጨምሮ ለተቋማት የተጠናከረ ሥልጣን ይሰጣል።

‍ ፖሊስ ለተጎጂዎች ተስማሚ አገልግሎቶችን በመጨመር፣ ልዩ የፆታዊ ጥቃት ዴስኮችን በማስተዋወቅ እና የ24 ሰዓት ጥበቃ ትዕዛዝ አገልግሎት በማስጀመር ጥረት እያደረገ መሆኑ ተጠቁሟል።

መሻሻሎች ቢኖሩም ትግበራው ያልተስተካከለ እና ወጥነት የጎደለው መሆኑን ራማፎሳ ተናግረዋል። በተሻለ መልኩ መከላከል እንዲቻል የወንዶች እና የወንድ ልጆች ቀጥተኛ ተሳትፎን ይጠይቃል ሲሉ አጽንዖት ሰጥተዋል።

“ወንዶችን በመከላከል ጥረቶች ውስጥ በቀጥታ ካላሳተፍን፤ [...] ቁጥሩ አይቀንስም። ወንዶች የፆታዊ ጥቃት እና የሴቶች ግድያ ወንጀል ዋና ፈፃሚዎች ቢሆኑም፤ የመፍትሄው አካልም ናቸው። ይህ የሴቶች ብቻ ትግል አይደለም።”

ቀውስን የሚያባብሱ መርዛማ የወንድነት ባህሪያትን እና ጎጂ ማህበራዊ ልማዶችን ለመጋፈጥ ሀገር አቀፍ ውይይቶች እንዲደረጉ ጥሪ አቅርበዋል።

“ሀገር አቀፍ አደጋ ሀገር አቀፍ ኃላፊነትን ይጠይቃል” በማለት፤ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች እና ዜጎች በድሏዊ ባህሪን እንዲገዳደሩ እና ጥቃት ሲፈፀም እንዲያሳውቁ አሳስበዋል። “የሴቶች እና ህፃናት ደህንነት የሁሉም ሰው ጉዳይ ነው።”

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0