ኢኮዋስ እና የአፍሪካ ኅብረት የቤኒን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ፈፃሚዎችን አወገዙ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢኮዋስ እና የአፍሪካ ኅብረት የቤኒን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ፈፃሚዎችን አወገዙ
ኢኮዋስ እና የአፍሪካ ኅብረት የቤኒን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ፈፃሚዎችን አወገዙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.12.2025
ሰብስክራይብ

ኢኮዋስ እና የአፍሪካ ኅብረት የቤኒን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ፈፃሚዎችን አወገዙ

የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማህበረሰብ የ "ሪፐብሊካን ጦር" ጥረቶችን በማድነቅ ለቤኒን መንግሥት ድጋፉን ገልጿል።

"ኢኮዋስ ይህን የቤኒን ሕዝብ ፍላጎት የናደ

ሕገ-ወጥ ድርጊት መናድ አጥብቆ ያወግዛል፤ ኢኮዋስ የመፈንቅለ መንግሥቱን መሪዎች በድርጊታቸው ለደረሠ ማንኛውም የህይወትና የንብረት መጥፋት በግለሰብ እና በጋራ ተጠያቂ ያደርጋል" ሲል አሳስቧል።

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሃሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፤ "በመፈንቅለ መንግሥቱ ሙከራ የተሳተፉ ሁሉም አካላት ሕገ-ወጥ ድርጊታቸውን ወዲያውኑ እንዲያቆሙ፣ የቤኒን ሕገ-መንግሥትን ሙሉ በሙሉ እንዲያከብሩ እና ያለምንም መዘግየት ወደ ሕጋዊ ተግባራቸው እና ሙያዊ ግዴታቸው እንዲመለሱ" አሳስበዋል።

"ሁሉም የሀገር ውስጥ ባለድርሻ አካላት አንድነትን፣ ውይይትን እና ብሔራዊ ሰላምን እንዲያስቀድሙ" አበረታተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0