ኢኮዋስ እና የአፍሪካ ኅብረት የቤኒን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ፈፃሚዎችን አወገዙ
20:02 07.12.2025 (የተሻሻለ: 20:54 07.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢኮዋስ እና የአፍሪካ ኅብረት የቤኒን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ፈፃሚዎችን አወገዙ
የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማህበረሰብ የ "ሪፐብሊካን ጦር" ጥረቶችን በማድነቅ ለቤኒን መንግሥት ድጋፉን ገልጿል።
"ኢኮዋስ ይህን የቤኒን ሕዝብ ፍላጎት የናደሕገ-ወጥ ድርጊት መናድ አጥብቆ ያወግዛል፤ ኢኮዋስ የመፈንቅለ መንግሥቱን መሪዎች በድርጊታቸው ለደረሠ ማንኛውም የህይወትና የንብረት መጥፋት በግለሰብ እና በጋራ ተጠያቂ ያደርጋል" ሲል አሳስቧል።
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሃሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው፤ "በመፈንቅለ መንግሥቱ ሙከራ የተሳተፉ ሁሉም አካላት ሕገ-ወጥ ድርጊታቸውን ወዲያውኑ እንዲያቆሙ፣ የቤኒን ሕገ-መንግሥትን ሙሉ በሙሉ እንዲያከብሩ እና ያለምንም መዘግየት ወደ ሕጋዊ ተግባራቸው እና ሙያዊ ግዴታቸው እንዲመለሱ" አሳስበዋል።
"ሁሉም የሀገር ውስጥ ባለድርሻ አካላት አንድነትን፣ ውይይትን እና ብሔራዊ ሰላምን እንዲያስቀድሙ" አበረታተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X