ብሪክስ በማደግ ላይ ላሉ ኢኮኖሚዎች ከጣልቃ ገብነት ነጻ የሆነ የልማት መንገድ ያቀርባል - ኢትዮጵያዊ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ
18:18 07.12.2025 (የተሻሻለ: 18:24 07.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ብሪክስ በማደግ ላይ ላሉ ኢኮኖሚዎች ከጣልቃ ገብነት ነጻ የሆነ የልማት መንገድ ያቀርባል - ኢትዮጵያዊ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ
የብሪክስ መነሳት ዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛኖችን ዳግም በመቅረጽ ባለብዝሃ ዋልታ ስርዓት ውስጥ ለአፍሪካ አዲስ መንገድ እያቀረበ ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ሞሀመድ ኢብራሂም ተናግረዋል።
ጥምረቱ ከንግድ ባለፈ ወደ ጂኦፖለቲካዊ መድረክ በማደግ እምቅ ወታደራዊ፣ የባሕር እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን እንደሚሸፍን ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።
የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ከምዕራባውያን በሀገራት ውስጣዊ ፖሊሲዎች ጣልቃ የመግባት አካሄድ ጋር በማነፃፀር፤ ብሪክስን ከጣልቃ ገብነት ነጻ የሆነ አማራጭ የልማት ሞዴል አድርገው እንደሚቆጥሩት ተናግረዋል።
"ብዙ ሀገራት፣ ብዙ ታዳጊ ኢኮኖሚዎች፤ በዚህ በብሪክስ ስርዓት ውስጥ መሳተፍ ይችላሉ ብዬ አምናለሁ። ስለዚህ መስፋፋቱ በእውነት ትልቅ ጠቀሜታ አለው" ብለዋል።
በብሪክስ አማካኝነት አፍሪካ ከእስያ ጋር ያላት ግንኙነት እያደገ መምጣቱ፤ ከፍተኛ የቴክኖሎጂ እና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖን እንደሚያሳይ በመጥቀስ፤ አህጉሪቱ የወደፊት የፈጠራ ማዕከልነት ዕጣ ፈንታዋን ይዛለች ብለው እንደሚያምኑ አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X