'ድርብ መስፈርትን በአንድነት በመታገል’ ለ57 ዓመታት የፀናው የሩሲያ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
15:28 07.12.2025 (የተሻሻለ: 15:34 07.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
'ድርብ መስፈርትን በአንድነት በመታገል’ ለ57 ዓመታት የፀናው የሩሲያ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
ሁለቱ ሀገራት "የቀደመ ወዳጃዊ ግንኙነት" እና የከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት ታሪክ አላቸው ሲል የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ገልጿል። ጠንካራ ግንኙነቱ ፕሬዝዳንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ንጌማ ምባሶጎ በመስከረም 2024 ወደ ሞስኮ ያደረጉትን ጉብኝት ያካትታል ሲል ጠቅሷል።
ሞስኮ እና ማላቦ "ባለብዝሃ ማዕከል የዓለም ስርዓት ሞዴል" ን ምርጫቸው በማድረግ፤ በዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ውስጥ "አሉታዊ ጫና እና ድርብ መስፈርቶችን" ይቃወማሉ እንዲሁም የሕዝቦችን የራሳቸውን የዕድገት መንገድ የመወሰን መብት ይደግፋሉ ሲል አመልክቷል።
የሁለቱ ሀገራት ተግባራዊ ትብብር ሩሲያ ከ1968 ጀምሮ ከአንድ ሺህ በላይ የኢኳቶሪያል ጊኒ ስፔሻሊስቶችን በማሠልጠን ያደረገችውን እገዛ ያካትታል። በ2024 የሩሲያ ኤምባሲ በማላቦ መከፈቱ ትልቅ እርምጃ እንደነበርም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X