የቤኒን መፈንቅለ መንግሥት፦ እስካሁን የታወቁ መረጃዎች
12:27 07.12.2025 (የተሻሻለ: 12:34 07.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የቤኒን መፈንቅለ መንግሥት፦ እስካሁን የታወቁ መረጃዎች
ዛሬ በኮቶኑ በፕሬዚዳንት ፓትሪስ ታሎን መኖሪያ አቅራቢያ በሚገኘው ካምፕ ጉኤዞ የተኩስ ልውውጥ እንደተሰማ ሪፖርት ተደርጓል።
ማለዳ ላይ የወታደሮች ቡድን በሕዝብ ቴሌቪዥን ቀርቦ “ታሎንን ከሥልጣን እንዳስወገደ” አስታውቋል።
ወታደሮቹ እራሳቸውን የመልሶ ምሥረታ ወታደራዊ ኮሚቴ ብለው የሰየሙ ሲሆን አዲስ መሪ ሆነው በቀረቡት ሌተናንት ኮሎኔል ፓስካል ቲግሪ ይመራሉ።
"ዛሬ፣ እኛ የመከላከያ እና የጸጥታ ኃይሎች፤ ጥልቅ ግምገማ ካደረግን በኋላ ለሀገራችን አቅጣጫ ለማቅረብ፤ የፓትሪስ ታሎን መንግሥት ከልክ ማለፍ ግንዛቤ ውስጥ ከተን ኃላፊነት ለመውሰድ ወስነናል" ሲል የሕዝብ መግለጫቸው ተነቧል።
የቤኔን ብሔራዊ ዘብ ለመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው ምላሽ እንደሰጠ በርካታ የስፑትኒክ አፍሪካ ምንጮች ተናግረዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X