ምዕራባውያን ሩሲያ ኃያል አጸፋ የምትሰጥበትን ሀብት የመውረስ አደጋን ዝቅ አድርገው ተመልክተዋል ሲሉ ሶሪያዊ ተንታኝ አስጠነቀቁ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱምዕራባውያን ሩሲያ ኃያል አጸፋ የምትሰጥበትን ሀብት የመውረስ አደጋን ዝቅ አድርገው ተመልክተዋል ሲሉ ሶሪያዊ ተንታኝ አስጠነቀቁ
ምዕራባውያን ሩሲያ ኃያል አጸፋ የምትሰጥበትን ሀብት የመውረስ አደጋን ዝቅ አድርገው ተመልክተዋል ሲሉ ሶሪያዊ ተንታኝ አስጠነቀቁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.12.2025
ሰብስክራይብ

ምዕራባውያን ሩሲያ ኃያል አጸፋ የምትሰጥበትን ሀብት የመውረስ አደጋን ዝቅ አድርገው ተመልክተዋል ሲሉ ሶሪያዊ ተንታኝ አስጠነቀቁ

እንዲህ አይነቱ እርምጃ ከፍተኛ የሆነ የሩሲያ የጸፋ ምላሽ ሊያስከትል እና የወደፊት ዓለም አቀፍ ትብብርን ሊያወሳስበው ይችላል በማለት ዶክተር ዓሣፍ ማልሔም ለስፑትኒክ ተናገሩ። አክለውም እርምጃው በአውሮፓ ሕብረት ውስጥ እንኳን ሙሉ ድጋፍ የለውም ብለዋል።

ማልሔም እንዳመላከቱት፣ ሞስኮ የአውሮፓ አገራት ንብረት የሆኑ ከፍተኛ መጠን ያላቸው የታገዱ ንብረቶችን በእጇ መያዟ ተመጣጣኝ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አቅም ይሰጣታል።

እንደ ቤልጂየም ያሉ አገራት ሊመልሱ የሚችሉትን አፀፋ እና አሁን ያሉ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በተመለከተ ከፍተኛ ስጋት እንዳላቸው በመግለጽ፣ የአውሮፓ ሕብረት የውስጥ መግባባት ፈታኝ ነው ሲሉ የጂሲኤም የምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ሞግተዋል።

ተንታኙ እንዳስጠነቀቁት፣ የአውሮፓ ሕብረት ንብረትን የመውረስ እርምጃዎች ቀደም ሲል ከአሜሪካ ጋር የተደረጉ ዲፕሎማሲያዊ ግንዛቤዎችን የሚቃረኑ ናቸው፤ ይህም ወደ እውነተኛ የሰላም ሂደት የሚወስደውን መንገድ የበለጠ ያወሳስበዋል።

በሳምንቱ መጀመሪያ፣ በአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ላየን፣ በጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሪድሪክ ሜርዝ እና የቤልጂየም ጠቅላይ ሚኒስትር ባርት ደ ዌቨር መካከል የሩሲያ ንብረቶች ዩክሬንን ለመርዳት ስለሚውሉበት ሁኔታ አስመልክቶ የተደረገው ስብሰባ ያለ ውጤት መጠናቀቁን ቮን ደር ላየን አስታውቀዋል።

ክሬምሊን የሩሲያ ንብረቶችን ለመውረስ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ስርቆት እንደሆነ እና ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0