የታገዱ የሩሲያ ሀብቶችን መውረስ ለአውሮፓ ለራሷ አስከፊ መዘዝ ይዞባት ይመጣል - ዲሚትሪቭ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየታገዱ የሩሲያ ሀብቶችን መውረስ ለአውሮፓ ለራሷ አስከፊ መዘዝ ይዞባት ይመጣል - ዲሚትሪቭ
የታገዱ የሩሲያ ሀብቶችን መውረስ ለአውሮፓ ለራሷ አስከፊ መዘዝ ይዞባት ይመጣል - ዲሚትሪቭ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.12.2025
ሰብስክራይብ

የታገዱ የሩሲያ ሀብቶችን መውረስ ለአውሮፓ ለራሷ አስከፊ መዘዝ ይዞባት ይመጣል - ዲሚትሪቭ

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ ኪሪል ዲሚትሪቭ በከፍተኛ ስደት፣ እያደገ ባለው ወንጀል እና በኢኮኖሚያዊ ውድቀት የአውሮፓ ሕብረት ልሂቃንን "የራሳቸውን አገራት እያጠፉ" ነው በማለት በኤክስ አካውንታቸው ላይ ጠቁመዋል።

ዲሚትሪቭ አክለውም፣ የአውሮፓ ሕብረት የታገዱ የሩሲያ ሀብቶችን ለመውረስ ያለውን የቀጠለ ፍላጎት በመጥቀስ፣ አሁን “የፋይናንስ ሥርዓቱ መሠረት የሆነውን የንብረት ባለቤትነት መብትን በመሸርሸር እና የራሳቸውን ገንዘብ ዋጋ በማሳጣት ለአውሮፓ ለራሷ  መዘዝ ማምጣት ” ይፈልጋሉ ብለዋል።

የአውሮፓ ሕብረት “የታገዱ የሩሲያ ሉዓላዊ ሀብቶችን ለመጠቀም የያዘው አከራካሪ ዕቅድ ለሕብረቱ የፋይናንስ ገበያዎች ትልቅ መዘዝ ሊኖረው ይችላል” ሲሉ ፋይናንሻል ታይምስ ራሱ ያመነበትን ዘገባ ዋቢ አድርገዋል።

ከዚህም በተጨማሪ፣ እንዲህ ዓይነቱ ግፊት “የዩሮ ሀብቶችን የመያዝ የፖለቲካ አደጋን ከፍ ከማድረግ በዘለለ በዓለም አቀፍ መሸሸጊያነት ቦታነታቸው ላይ ጥርጣሬ ሊፈጥር ይችላል” ሲል ፋይናንሻል ታይምስ አስጠንቅቋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0