የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት 'የሕግ ቅኝ ግዛት መሣሪያ' መሆኑን የቬኔዙዌላ ከአባልነት መልቀቅ ያሳያል
16:46 06.12.2025 (የተሻሻለ: 16:54 06.12.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት 'የሕግ ቅኝ ግዛት መሣሪያ' መሆኑን የቬኔዙዌላ ከአባልነት መልቀቅ ያሳያል
ቬኔዙዌላ ወጥነት በሌለው፣ በአድልዎ እንዲሁም የፖለቲካ የበላይነት ፍላጎቶች በማገልገል የተከሰሰውን ዓለም አቀፍ የፍትሕ ስርዓት በመቃወም ራሷን ለመከላከል ሉዓላዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው ሲሉ ቬኔዙዌላዊቷ የሕግ ባለሙያ አና ክሪስቲና ብራቾ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
ባለፈው ሳምንት፣ የቬኔዙዌላ ብሔራዊ ምክር ቤት የሮም ስምምነትን የሚያወግዝ እና አገሪቱን ከዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይሲሲ) ሥልጣን የሚያስወጣ ረቂቅ ሕግ በመጀመሪያ ንባብ አጽድቋል።
ይህ ተነሳሽነት የመጣው ረቂቅ ሕጉን ያቀረቡት ግለሰብ ፍርድ ቤቱ ወደ “የኢምፔሪያሊስት እና የቅኝ ገዥ ፍላጎቶች መሣሪያነት" መለወጡን እና ዓለም አቀፍ ፍትሕን ከማስከበር ይልቅ በደቡብ አሜሪካዊቷ አገር ላይ “ማሳደድ” መፈጸሙን በመግለጻቸው ነው።
ይህ ጉዳይ ከቬኔዙዌላ ባሻገር በተደጋጋሚ ቅሬታ የቀረበበት መሆኑን ብራቾ አስታውሰዋል።
“ለአስር ዓመታት ያህል፣ የአፍሪካ አገራት ይህ ተቋም 'የነጮች ፍርድ ቤት' ሆኗል፣ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የሚፈጸሙት በእነሱ ግዛት ላይ ብቻ እንደሆነ ሁሉ ጥቁር ሕዝብ ያላቸውን አገራት ብቻ በመክሰስ ላይ ነው ሲሉ ቆይተዋል። በተጨማሪም እንደ አሜሪካ፣ ቻይና እና ሩሲያ ያሉ ታላላቅ ኃይሎች የዚህ ተቋም አካል አለመሆናቸውን እንመለከታለን። በዚህም ምክንያት የዓለም አብዛኛው ክፍል በሥልጣኑ ስር አይጠቃለልም” ሲሉ አብራርተዋል።
ብራቾ አገሪቱ ከዚህ አካል መውጣቷ ለካራካስ ሊኖረው የሚችለውን አንድ ውጤት ሲገመግሙ “ለወደፊቱ በቬኔዙዌላ ላይ አዲስ ምርመራዎች ሊከፈቱ አይችሉም” የሚል ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X