ከኢትዮጵያ ከ50 ሚሊዮን በላይ የገበሬ ማሳዎች ውስጥ፣ 32 ሚሊዮኑ ተለይተው ተመዝግበዋል – ግብርና ሚኒስቴር
20:06 05.12.2025 (የተሻሻለ: 20:14 05.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ከኢትዮጵያ ከ50 ሚሊዮን በላይ የገበሬ ማሳዎች ውስጥ፣ 32 ሚሊዮኑ ተለይተው ተመዝግበዋል – ግብርና ሚኒስቴር
ለ10.5 ሚሊዮን አባወራዎች የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት መሰጠቱንም የአገር ውስጥ ሚዲያ የሚኒስቴሩን ባለሥልጣን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
ባለፉት ዓመታት የተገነባው ብሔራዊ የገጠር መሬት መረጃ ሥርዓት አሁን ላይ በ516 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረጉንም ተገልጿል፡፡
የአርሶ አደሮች የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ለውርስ፣ ለማከራየት እንዲሁም ከፋይናንስ ተቋማት የብድር አገልግሎት ማግኘት እንደሚያስችል ዘገባው አመላክቷል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X