የፑቲን የሕንድ ጉብኝት የጂኦፖለቲካዊ ጠቅላይነትን የሚፈታተን እና ብሪክስ-መር 'ዶላርን አለመጠቀምን' እንቅስቃሴ ያፋጥናል - ሱዳናዊ ተንታኝ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየፑቲን የሕንድ ጉብኝት የጂኦፖለቲካዊ ጠቅላይነትን የሚፈታተን እና ብሪክስ-መር 'ዶላርን አለመጠቀምን' እንቅስቃሴ ያፋጥናል - ሱዳናዊ ተንታኝ ተናገሩ
የፑቲን የሕንድ ጉብኝት የጂኦፖለቲካዊ ጠቅላይነትን የሚፈታተን እና ብሪክስ-መር 'ዶላርን አለመጠቀምን' እንቅስቃሴ ያፋጥናል - ሱዳናዊ ተንታኝ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.12.2025
ሰብስክራይብ

የፑቲን የሕንድ ጉብኝት የጂኦፖለቲካዊ ጠቅላይነትን የሚፈታተን እና ብሪክስ-መር 'ዶላርን አለመጠቀምን' እንቅስቃሴ ያፋጥናል - ሱዳናዊ ተንታኝ ተናገሩ

የሩሲያ ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር አቦባክር መሐመድ አባከር ኩሴን ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፣ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ጉብኝት ለጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ “ወሳኝ ጊዜ” ላይ የመጣ ነው። የምዕራባውያን ጫናዎች ቢኖሩም፣ ጉብኝቱ “ሁለቱንም አሸናፊ የሚያደርግ”፣ "በአጋርነት" እና “በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ ንግድን” ያረጋገጠ ነው።

እንደ ኩሴን ገለጻ፣ ከጉብኝቱ የተገኙ ቁልፍ ስልታዊ ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦

በኢኮኖሚ መለያየት (ራስን መቻል) እና ንግድ፦ በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የሁለትዮሽ ንግድ ከተያዘለት ጊዜ በሦስት ዓመታት ቀድሞ 30 ቢሊዮን መድረሱን፣ ይህም በሕንድ “ቅናሽ የተደረገባቸውን የሩሲያ የኢነርጂ ምርቶች” በማስገባት እና የመድኃኒትና የማሽን ምርቶችን በመላክ የተጠናከረ በመሆኑ፣ ሁለቱ አገራት እ.ኤ.አ. 2030 ድረስ 100 ቢሊዮን የንግድ ልውውጥ ለማድረግ አቅደዋል ብለዋል።

የዲዶላራይዜሽን ፍጥነት መጨመር፦ አሁን ያለው የሩሲያ-ሕንድ ንግድ ወደ 100 በመቶ የሚጠጋው በብሔራዊ ገንዘቦች እየተካሄደ ነው ያሉት ኩሴን፣ “አሜሪካ ዶላርን እንደ መሣሪያ የመጠቀም ፖሊሲ የመልስ ምት ” ውጤት ነው ብለዋል።

የሕዋ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት፦ በጋራ የሚካሄዱት የሮኬት-ሞተር ፕሮግራሞች እና በብሔራዊ የጠፈር ጣቢያዎች መካከል ያለው የምኅዋር ትብብር ለደቡባዊ ዓለም ቴክኖሎጂያዊ ነፃነትን ለማጎልበት እና በሕዋ አስተዳደር ውስጥ ያለውን የአሜሪካና የአውሮፓ የበላይነት ለማመጣጠን ታስቦ የተሠራ ነው።

ለደቡባዊ ዓለም የሚሆን ሞዴል፦ አፍሪካ በብዙ-አገራት መድረኮች በቡድን በመምረጥ፣ በእውቀት ምርት እንዲሁም በባሕል ትርክቶች ላይ ቁጥጥርን በመመለስ የፖለቲካ ሉዓላዊነቷን ተግባራዊ በማድረግ ከሕንድ የተነሳሽነት አብነትን መውሰድ ትችላለች ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አባካር ኩሴን ሲያጠቃልሉ፣ “ብሪክስ ከቀድሞ ቡድን 8 (የአሁን ቡድን 7) የበለጠ ለሩሲያ ጠቃሚ ነው፤ በዋነኛነት ለምዕራባውያን ማዕቀቦች ኢኮኖሚያዊ አማራጮችን ስለሚሰጥ፣ ከምዕራባውያን ውጪ ካሉ ኃያላን ጋር ዲፕሎማሲያዊ መድረኮችን ስለሚያቀርብ እና ለብዝኃ-ዋልታ ዓለም መሠረት ስለሚጥል ነው” ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0