በኦጋዱጉ ለሦስት ቀናት የሚቆይ የመሬት እና የባሕር ትራንስፖርት ባለድርሻ አካላት ጠቅላላ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ
18:47 04.12.2025 (የተሻሻለ: 18:54 04.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኦጋዱጉ ለሦስት ቀናት የሚቆይ የመሬት እና የባሕር ትራንስፖርት ባለድርሻ አካላት ጠቅላላ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ
የቡርኪና ፋሶ ትራንስፖርት የሕዝብና የግል ዘርፍ ተዋናዮች፣ ከቴክኒክና ፋይናንስ አጋሮች ጋር በመሆን፣ በአገሪቱ ውስጥ ስላለው አስከፊ ሁኔታ አስጠንቅቀዋል፡፡ የተበላሹ መንገዶች፣ የተተዉ ባቡሮች፣ ያረጁ ተሽከርካሪዎች፣ አነስተኛ ዲጂታላይዜሽን እና ፈንድ የማግኘት ዕድል እጅግ አስቸጋሪ መሆኑ ገልፀዋል።
ለዋና ዋና ማሻሻያዎች የቀረቡ ቁልፍ ምክረ ሐሳቦች የሚከተሉትን ያካትታሉ፡-
ዋና ዋና የመንገድ ኮሪደሮችን በአስቸኳይ ማደስ እና አስተማማኝ የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችን መገንባት፣
የኤሌክትሮኒክስ ቲኬት አሰጣጥ፣ ጂፒኤስ መከታተያ፣ አውቶማቲክ የሻንጣ አያያዝን ሙሉ ለሙሉ ዲጂታል ማድረግ፣
የጭነት መኪናዎችንና አውቶቡሶችን ለማደስ የሚያስችል ብሔራዊ ፈንድ ማቋቋም፣
የባቡር መስመሩን ሙሉ በሙሉ ማደስ እና የባቡር መስመሮቹን ወደ ጎረቤት አገራት ማስፋፋት እና
በከተማዋ ያለውን መጨናነቅ ለመቀነስ በዋጋዱጉ የጭነት መኪናዎች የሚንቀሳቀሱበትን ሰዓት ማራዘም።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X