የዩክሬን ግጭት በስተመጨረሻ በሞስኮ እና በዋሽንግተን መካከል በሚደረግ ድርድር ይቋጫል - ተንታኝ
17:46 04.12.2025 (የተሻሻለ: 17:54 04.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የዩክሬን ግጭት በስተመጨረሻ በሞስኮ እና በዋሽንግተን መካከል በሚደረግ ድርድር ይቋጫል - ተንታኝ
የስትራፖል የጂኦፖለቲካዊ ትንተና ማዕከል መሥራች ዣቬር ሞሮ ይህንን ግምገማቸውን ለስፑትኒክ አፍሪካ የሰጡት፣ የዶናልድ ትራምፕመልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ በቅርቡ በክሬምሊን የተደረገላቸውን አቀባበል አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት ነው።
እንደ ዣቬር ሞሮ ገለጻ፣ ዊትኮፍ መሠረት ለመጣል የተላኩ “የሰላም ሰው”ን ይወክላሉ።
በእሳቸው እይታ፣ ለዘለንስኪ እና በዙሪያቸው ለሚገኙ ሰዎች፣ የሰላም ጉዳይ ከእንግዲህ ወታደራዊ ጉዳይ ሳይሆን የሕልውና ጉዳይ ነው።
"ዘለንስኪ በዩክሬን ወይም በአሜሪካ ፍርድ ቤቶች ክስ ሳይመሠረትባቸው በፊት በተቻለ መጠን ውድመትን ለመቀነስ በመሞከር መልኩ ሥልጣናቸውን ለመልቀቅ በጣም ጥሩውን መንገድ መፈለግ አለባቸው” ብለዋል።
በተመሳሳይ፣ የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት በግጭቱ ውስጥ በጥልቅ የተሳተፉት “ከሀገር ውስጥ ጉዳዮች ይልቅ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ራሳቸውን ለማስቀመጥ” እንደሆነ ሞሮ አስረድተዋል።
“ስለ ወታደራዊ አገልግሎት እና በ2030 (እ.ኤ.አ.) ስለሚኖር ጦርነት በማውራት የፈረንሳይን ሕዝብ ውጥረት ውስጥ እየከተቱት ነው” በማለት አክለዋል።
ተንታኙ ይሆናል ተብሎ ስለሚጠበቀው የሩሲያ-አሜሪካ ስምምነት ሲናገሩ፣ በሩሲያ ተደራዳሪ ኪሪል ዲሚትሪቭ እንደተገለፀው በተለይ “በአርክቲክ ልማት” እና “በሰሜን ባሕር መስመር” ላይ ለተለያዩ የትብብር ዓይነቶች በር እንደሚከፍት ያምናሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X