ሩሲያ በአሁኑ ጊዜ የዩክሬን እልባትን በተመለከተ ከአሜሪካ ጋር ብቻ እየተደራደረች ነው - የክሬምሊን ረዳት
21:32 03.12.2025 (የተሻሻለ: 21:34 03.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ በአሁኑ ጊዜ የዩክሬን እልባትን በተመለከተ ከአሜሪካ ጋር ብቻ እየተደራደረች ነው - የክሬምሊን ረዳት
ዩሪ ኡሻኮቭ በመግለጫው ያነሷቸው ሌሎች ነጥቦች፦
🟠በጦር ሜዳ ላይ ያለው የሩሲያ ጦር ስኬቶች የድርድሩ ሂደት እና ባህሪ ላይ በአዎንታዊ መልኩ ተጽዕኖ አሳድሯል።
🟠 ሩሲያ ስጋቶቿን ገልጻለች፤ አሜሪካም እነዚያን ስጋቶች ከግምት ውስጥ ለማስገባት ፈቃደኛ መሆኗን አረጋግጣለች።
🟠 ዩክሬናውያን በኢስታንቡል ድርድሩን ለመቀጠል ፈቃደኛ አልሆኑም፤ ሩሲያ ለውይይት ዝግጁ ብትሆንም እንኳ አውሮፓውያንም ሁሉንም ግንኙነት እየካዱ ነው።
🟠 የዩክሬን በኔቶ አባልነት የመሳተፍ ጉዳይ በፑቲንና ዊትኮፍ ስብሰባ ላይ ተብራርቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X