- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የሀገር-በቀል እውቀት፡ የማንነት እና የስነ-ልኬታችን መሣሪያ

የሀገር-በቀል እውቀት፡ የማንነት እና የስነ-ልኬታችን መሣሪያ
ሰብስክራይብ

“የሀገር-በቀል እውቀት የስነ-ልኬታችን መሳሪያ ነው [...] የአንድ ሰው፣ የአንድ ህዝብ፣ የአንድ ሃገር የጥሩ እና የመጥፎ ነገር መለኪያ ማለት ነው፡፡ ይሄ መጥፎ ነው፣ ይሄ ጥሩ ነው፣ ይሄ ይሻላል፣ ይሄ አይሻልም፣ ይሄ ይበልጣል ይሄ አይበልጥም ብሎ ህዝብ የሚበይንበት፣ የሚለካበት፣ ያሉትን እሴቶች የሚለካበት ነው፡፡ እሱ የለህም ማለት መለኪያህን ተነጠቅህ ማለት ነው፡፡ መለኪያህ ካንተ ወጣ ማለት በሌሎች መለኪያ ውስጥ ትገባለህ፡፡” ሲሉ በሀገር-በቀል እውቀት ጥናት እና ምርምር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ አብዱልፈታህ አብደላህ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የሀገር-በቀል እውቀት በመደበኛው የትምህርት-ሥርዓት ውስጥ ያለመካተቱን ምስጢር በሀገር-በቀል እውቀት ጥናት እና ምርምር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ አብዱልፈታህ አብደላህ በሰፊው አብራርተውታል፡፡ በተጭማሪም በምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካ ውስጥ ከፍተኛ የመነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ እየሆነ ስለመጣው የቀይ ባህር ጉዳይ የታሪክ ተመራማሪ ከሆኑት ከፕሮፌሰር አህመድ ዘካሪያ ያደረግነውም ውይይት በዚህ ዝግጅት ውስጥ ተካትቷል፡፡

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0